የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የጤና አገልግሎትን የሚያሳልጡ የቴክኖሎጂ ውጤቶች

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ )በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽን እና ጥራት ጉባኤ ላይ አገልግሎትን የሚያዘምኑና ተደራሽነትን የሚያሰፉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለአውደ ርዕይ ቀርበዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነነት አስተዳደር የድሮን ቴክኖሎጂ በመጠቀም መድሃኒት ማድረስና የኬሚካል ርጭት አገልግሎት መስጠት የሚችሉ የፈጠራ ውጤቶችን አቅርቧል።


በአስተዳደሩ የፕሮጀክት ማናጀር ካሳ አጠና ድሮኖቹ ከጤና እና ግብርና ዘርፎች ጋር የተያያዙ አገልግሎቶችን ማቅረብ የሚችሉ እንደሆኑ አብራርተዋል።

በጤናው ዘርፍ የጸረ-ወባ ኬሚካል ርጭት፣ መድሃኒትን የማድረስና ሌሎች አገልግሎቶችን በፍጥነት መስጠት የሚችሉ እንደሆኑ አስረድተዋል።


በተመሳሳይ በግብርናው ዘርፍም የጸረ-አረም ርጭት አገልግሎትን መስጠት የሚችሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ናቸው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ፈጣን የጤና አገልግሎትና የህሙማንን ደህንነት ከማስጠበቅ አንጻር የድሮን ቴክኖሎጂ ፈጣን አገልግሎት በማቅረብ አገልግሎትን እንደሚያሳልጥ ነው የተናገሩት።

በአሁኑ ወቅት በተወሰኑ የአገሪቱ አካባቢዎች መድሃኒቶችን በማድረስ አገልግሎት እየሰጡ እንደሆነ ገልጸው የግል ባለሃብቶች በዘርፉ ኢንቨስት ቢያድርጉ ለጤናው ዘርፍ አገልግሎት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ጠቁመዋል።

የአለርት ሆስፒታል በቀዶ ጥገና ወቅት ሂደቱን ለምርምርና ለማስተማሪያ ቀርጾ የሚያስቀምጥ የቴክኖሎጂ ውጤት አቅርቧል።

የቀዶ ጥገና ክፍል ነርስ ናትናኤል ብርሃኑ ቴክኖሎጂው የቀዶ ጥገና ሂደትን ለምርምር፣ ለማስተማሪያነትና ምክረ ሃሳብን ከባለሙያዎች በቀጥታ ለማግኘት የሚያስችል እንደሆነ አብራርቷል።



ለሆስፒታሎች ወረቀት አልባ አሰራርን በማልማት ያቀረበው ኢ-ቴክ የተሰኘ ተቋም ከፍተኛ የማርኬቲንግ ባለሙያ ደሳለኝ ዋሚ አሰራሩ የታካሚዎችና ህክምና ተቋማትን መረጃ ልውውጥ የሚያሳልጥ እንደሆነ አመላክቷል።


በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎትን በኢኖቬሽን የሚደግፉ የመንግስት እና የግል ተቋማት የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶቻቸውን በአውደ ርዕዩ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026