የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በመዲናዋ በኢንዱስትሪ፣ ንግድና በተለያዩ ዘርፎች በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ አለ - አቶ ጥራቱ በየነ

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በኢንዱስትሪ ንግድና በተለያዩ ዘርፎች በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንዳለ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ባስጠናው የፀጋ ልየታ አሰራር ጋይድላይን እና የስራ ዕድል መፍጠሪያ መስኮች ጥናት ላይ ለዘርፉ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።


በስልጠናው መክፈቻ መርሃ ግብር የተገኙት የከተማ አስተዳደሩ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ እንደገለጹት፤ ስልጠናው በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ የዘርፉ አመራርና ባለሙያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችል ነው።

መዲናዋ ትልቅ ጸጋ ያላት እንደመሆኗ መጠን በኢንዱስትሪ፤ በንግድና በተለያዩ ዘርፎች በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንዳለ ተናግረዋል።

መድረኩ በቀጣይ ዓመት በተሻለ እውቀትና መረጃ ላይ በመመሰረት ለወጣቱ ቋሚ የስራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አቅም እንድሚሆን ገልጸዋል።


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር እና የጥናት ቡድኑ መሪ ጆንሴ ባኔ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጥናቱ ዋና ዓላማ በከተማዋ የስራ ዕድል ዘርፎችን ለመለየት መሆኑን ተናግረዋል።

ይህን የስራ ዕድል ለመፍጠር በጥናት የታገዙና መረጃን መሰረት ያደረጉ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

ከስልጠናው ተሳታፊዎች መከካል አቶ ናሆም ለማ ጥናቱ የስራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አቅም እንደሚሆን አመልክተዋል።


ጥናቱ በደንብ ከተሰራበት በከተማዋ የስራ ዘርፎችን በመለየት በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር ያስችላል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያያት ሰጪ አቶ ኢብራሂም መሀመድ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.