
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በኢንዱስትሪ ንግድና በተለያዩ ዘርፎች በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንዳለ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ ገለጹ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ባስጠናው የፀጋ ልየታ አሰራር ጋይድላይን እና የስራ ዕድል መፍጠሪያ መስኮች ጥናት ላይ ለዘርፉ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።

በስልጠናው መክፈቻ መርሃ ግብር የተገኙት የከተማ አስተዳደሩ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ እንደገለጹት፤ ስልጠናው በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ የዘርፉ አመራርና ባለሙያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችል ነው።
መዲናዋ ትልቅ ጸጋ ያላት እንደመሆኗ መጠን በኢንዱስትሪ፤ በንግድና በተለያዩ ዘርፎች በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንዳለ ተናግረዋል።
መድረኩ በቀጣይ ዓመት በተሻለ እውቀትና መረጃ ላይ በመመሰረት ለወጣቱ ቋሚ የስራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አቅም እንድሚሆን ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር እና የጥናት ቡድኑ መሪ ጆንሴ ባኔ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጥናቱ ዋና ዓላማ በከተማዋ የስራ ዕድል ዘርፎችን ለመለየት መሆኑን ተናግረዋል።
ይህን የስራ ዕድል ለመፍጠር በጥናት የታገዙና መረጃን መሰረት ያደረጉ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
ከስልጠናው ተሳታፊዎች መከካል አቶ ናሆም ለማ ጥናቱ የስራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አቅም እንደሚሆን አመልክተዋል።

ጥናቱ በደንብ ከተሰራበት በከተማዋ የስራ ዘርፎችን በመለየት በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር ያስችላል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያያት ሰጪ አቶ ኢብራሂም መሀመድ ናቸው።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026