
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በኢንዱስትሪ ንግድና በተለያዩ ዘርፎች በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንዳለ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ ገለጹ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ባስጠናው የፀጋ ልየታ አሰራር ጋይድላይን እና የስራ ዕድል መፍጠሪያ መስኮች ጥናት ላይ ለዘርፉ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።

በስልጠናው መክፈቻ መርሃ ግብር የተገኙት የከተማ አስተዳደሩ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ እንደገለጹት፤ ስልጠናው በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ የዘርፉ አመራርና ባለሙያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችል ነው።
መዲናዋ ትልቅ ጸጋ ያላት እንደመሆኗ መጠን በኢንዱስትሪ፤ በንግድና በተለያዩ ዘርፎች በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንዳለ ተናግረዋል።
መድረኩ በቀጣይ ዓመት በተሻለ እውቀትና መረጃ ላይ በመመሰረት ለወጣቱ ቋሚ የስራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አቅም እንድሚሆን ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር እና የጥናት ቡድኑ መሪ ጆንሴ ባኔ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጥናቱ ዋና ዓላማ በከተማዋ የስራ ዕድል ዘርፎችን ለመለየት መሆኑን ተናግረዋል።
ይህን የስራ ዕድል ለመፍጠር በጥናት የታገዙና መረጃን መሰረት ያደረጉ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
ከስልጠናው ተሳታፊዎች መከካል አቶ ናሆም ለማ ጥናቱ የስራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አቅም እንደሚሆን አመልክተዋል።

ጥናቱ በደንብ ከተሰራበት በከተማዋ የስራ ዘርፎችን በመለየት በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር ያስችላል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያያት ሰጪ አቶ ኢብራሂም መሀመድ ናቸው።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026