የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ጃይካ በኢትዮጵያ እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ ይቀጥላል

Jul 1, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ(ጃይካ) በኢትዮጵያ እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ የጃይካ ተወካይ ኬንሱኬ ኦሺማ ገለፁ።

ጃይካ ከኢትዮጵያ ጋር ለዘመናት የዘለቀ የልማት ትብብር እንዳለው ለኢዜአ የገለጹት ተወካዩ፥ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች በርካታ ለውጦችን እንዳመጡ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።

ጃይካ በግብርናና ገጠር ልማት፣ በመሰረተ ልማት፣ ኢንዱስትሪያላይዜሽንና በትምህርት ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

የገበያ ተኮር ግብርና፣ የሩዝ ምርታማነትና የውሃ ዘርፍ ልማትም ጃይካ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ከሚሰራባቸው የትብብር መስኮች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

ጃይካ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና ሌሎች ዘርፎች ላይ በትብብር እየሰራ መሆኑንና እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ለውጥ እያስመዘገቡ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የስኬት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመላ ሀገሪቱ መሰል የልማት ስራዎችን ለማጠናከር እየተሰራ ያለውን ስራ ጃይካ እንደሚደግፍም ተወካዩ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.