
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ(ጃይካ) በኢትዮጵያ እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ የጃይካ ተወካይ ኬንሱኬ ኦሺማ ገለፁ።
ጃይካ ከኢትዮጵያ ጋር ለዘመናት የዘለቀ የልማት ትብብር እንዳለው ለኢዜአ የገለጹት ተወካዩ፥ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች በርካታ ለውጦችን እንዳመጡ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።
ጃይካ በግብርናና ገጠር ልማት፣ በመሰረተ ልማት፣ ኢንዱስትሪያላይዜሽንና በትምህርት ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የገበያ ተኮር ግብርና፣ የሩዝ ምርታማነትና የውሃ ዘርፍ ልማትም ጃይካ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ከሚሰራባቸው የትብብር መስኮች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ጃይካ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና ሌሎች ዘርፎች ላይ በትብብር እየሰራ መሆኑንና እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ለውጥ እያስመዘገቡ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የስኬት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመላ ሀገሪቱ መሰል የልማት ስራዎችን ለማጠናከር እየተሰራ ያለውን ስራ ጃይካ እንደሚደግፍም ተወካዩ አረጋግጠዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026