
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ(ጃይካ) በኢትዮጵያ እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ የጃይካ ተወካይ ኬንሱኬ ኦሺማ ገለፁ።
ጃይካ ከኢትዮጵያ ጋር ለዘመናት የዘለቀ የልማት ትብብር እንዳለው ለኢዜአ የገለጹት ተወካዩ፥ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች በርካታ ለውጦችን እንዳመጡ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።
ጃይካ በግብርናና ገጠር ልማት፣ በመሰረተ ልማት፣ ኢንዱስትሪያላይዜሽንና በትምህርት ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የገበያ ተኮር ግብርና፣ የሩዝ ምርታማነትና የውሃ ዘርፍ ልማትም ጃይካ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ከሚሰራባቸው የትብብር መስኮች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ጃይካ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና ሌሎች ዘርፎች ላይ በትብብር እየሰራ መሆኑንና እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ለውጥ እያስመዘገቡ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የስኬት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመላ ሀገሪቱ መሰል የልማት ስራዎችን ለማጠናከር እየተሰራ ያለውን ስራ ጃይካ እንደሚደግፍም ተወካዩ አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026