
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ በስፔን ሲቪያ እየተካሔደ ባለው አራተኛው አለም ዓቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፈረንስ ላይ በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልኡክ እየተሳተፈ ይገኛል።
ኮንፈረንሱ እኤአ ከጁን 30 እስከ ጁላይ 3/2025 እንደሚካሔድም ታውቋል።
የልዑክ ቡድኑ በኮንፈረንሱ በሚያደርገው ተሳትፎ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ኢትዮጵያን በመወከል ተሳትፎ የሚያደርግ ይሆናል።
ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን Global Alliance Against Poverty and Hunger የትይዩ ስብሰባ ያዘጋጀ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በብራዚል የG20 ሊቀ መንበርነት የተቋቋመው የዚሁ Alliance የሻምፕዮኖች የቦርድ አባል እንደመሆኗ በሌማት ትሩፋት ዙሪያ ያላት ልምድ እንደ ተምሳሌታዊ ፕሮጀክት በግብርና ሚኒስትሩ በኩል ይቀርባል።

ኢትዮጵያ በሌማት ትሩፋት ያስመዘገበችውን ውጤት በኮንፈረንሱ ላይ በተሞክሮነት ከማጋራት በተጨማሪ ሀገራችን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የምታደርጋቸውን ሌሎች ሰፋፊ ጥረቶች ሚኒስትሩ እንደ ልምድ የሚያቀርቡ ይሆናል።
አራተኛው አለም ዓቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፈረንስ የዘላቂ ልማት ግቦችን እ.አ.አ በ2030 ለማሳካት በዋነኛነት ማነቆ የሆነውን የልማት ፋይናንስ ተግዳሮት ለመፍታት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሚኒስቴሩ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያሳያል።
ሶስተኛው አለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ እ.አ.አ በ2015 በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወሳል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026