የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ በአራተኛው የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፈረንስ ላይ እየተሳተፈች ትገኛለች

Jul 1, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ በስፔን ሲቪያ እየተካሔደ ባለው አራተኛው አለም ዓቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፈረንስ ላይ በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልኡክ እየተሳተፈ ይገኛል።

ኮንፈረንሱ እኤአ ከጁን 30 እስከ ጁላይ 3/2025 እንደሚካሔድም ታውቋል።

የልዑክ ቡድኑ በኮንፈረንሱ በሚያደርገው ተሳትፎ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ኢትዮጵያን በመወከል ተሳትፎ የሚያደርግ ይሆናል።

ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን Global Alliance Against Poverty and Hunger የትይዩ ስብሰባ ያዘጋጀ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በብራዚል የG20 ሊቀ መንበርነት የተቋቋመው የዚሁ Alliance የሻምፕዮኖች የቦርድ አባል እንደመሆኗ በሌማት ትሩፋት ዙሪያ ያላት ልምድ እንደ ተምሳሌታዊ ፕሮጀክት በግብርና ሚኒስትሩ በኩል ይቀርባል።


ኢትዮጵያ በሌማት ትሩፋት ያስመዘገበችውን ውጤት በኮንፈረንሱ ላይ በተሞክሮነት ከማጋራት በተጨማሪ ሀገራችን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የምታደርጋቸውን ሌሎች ሰፋፊ ጥረቶች ሚኒስትሩ እንደ ልምድ የሚያቀርቡ ይሆናል።

አራተኛው አለም ዓቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፈረንስ የዘላቂ ልማት ግቦችን እ.አ.አ በ2030 ለማሳካት በዋነኛነት ማነቆ የሆነውን የልማት ፋይናንስ ተግዳሮት ለመፍታት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሚኒስቴሩ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያሳያል።

ሶስተኛው አለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ እ.አ.አ በ2015 በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026