
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ በስፔን ሲቪያ እየተካሔደ ባለው አራተኛው አለም ዓቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፈረንስ ላይ በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልኡክ እየተሳተፈ ይገኛል።
ኮንፈረንሱ እኤአ ከጁን 30 እስከ ጁላይ 3/2025 እንደሚካሔድም ታውቋል።
የልዑክ ቡድኑ በኮንፈረንሱ በሚያደርገው ተሳትፎ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ኢትዮጵያን በመወከል ተሳትፎ የሚያደርግ ይሆናል።
ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን Global Alliance Against Poverty and Hunger የትይዩ ስብሰባ ያዘጋጀ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በብራዚል የG20 ሊቀ መንበርነት የተቋቋመው የዚሁ Alliance የሻምፕዮኖች የቦርድ አባል እንደመሆኗ በሌማት ትሩፋት ዙሪያ ያላት ልምድ እንደ ተምሳሌታዊ ፕሮጀክት በግብርና ሚኒስትሩ በኩል ይቀርባል።

ኢትዮጵያ በሌማት ትሩፋት ያስመዘገበችውን ውጤት በኮንፈረንሱ ላይ በተሞክሮነት ከማጋራት በተጨማሪ ሀገራችን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የምታደርጋቸውን ሌሎች ሰፋፊ ጥረቶች ሚኒስትሩ እንደ ልምድ የሚያቀርቡ ይሆናል።
አራተኛው አለም ዓቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፈረንስ የዘላቂ ልማት ግቦችን እ.አ.አ በ2030 ለማሳካት በዋነኛነት ማነቆ የሆነውን የልማት ፋይናንስ ተግዳሮት ለመፍታት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሚኒስቴሩ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያሳያል።
ሶስተኛው አለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ እ.አ.አ በ2015 በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወሳል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026