
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ተግባራዊ የተደረጉ ኢኒሼቲቮች በተጨባጭ የሕብረተሰቡን ሕይወት እየቀየሩ መሆናቸውን በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ገለጹ።
በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ቡድን በምዕራብ ጉጂ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን እየጎበኘ ነው።
በጉብኝቱም የስንዴ ክላስተር፣ የቀበሌ አስተዳደር አደረጃጀት፣ የባህላዊ ፍርድ ቤት፣ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጨምሮ ሌሎችም ተጎብኝተዋል።


ጉብኝቱን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ፤ በኦሮሚያ ክልል የስንዴ፣ የማር፣ የአረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በርካታ ኢኒሼቲቮች ተግባራዊ እየተደረጉ ነው።
እነኚህ ኢኒሼቲቮችም አስፈላጊ የሚባሉ ዝግጅቶች ተደርገው ወደ ስራ የገቡ መሆኑን ጠቁመው በተጨባጭ የሕብረተሰቡን ሕይወት በመቀየር ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ለአብነትም በምዕራብ ጉጂ ዞን በክላስተር በመልማት ላይ የሚገኘው የስንዴ እና የጤፍ ምርታማነት በእጅጉ መጨመሩን ተናግረዋል።

ለዚህም መንግስት አስፈላጊ የሚባሉ የግብርና ግብዓቶችን በማቅረብ ለውጤታማነቱ አስፈላጊውን ሁሉ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የአርሶ አደሩ ህይወት በተጨባጭ እየተቀየረ መሆኑን አንስተዋል።
በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው የቀበሌ አደረጃጀት የህብረተሰቡን እንግልት በተግባር ያስቀረ፤ አገልግሎት በአካባቢያቸው እንዲያገኙ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።
በምዕራብ ጉጂ ዞንም የቀበሌ አስተዳደር ጽህፈት ቤቶች በተቀመጠው ስታንዳርድ መሠረት ተገንብተው ለሕብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በምዕራብ ጉጂ ዞን ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነቡ የሚገኙ የውሃ ፕሮጀክቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንደሚሰጡ ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በክልሉ ተግባራዊ የተደረጉ ኢኒሼቲቮች የአርሶ አደሩን ሕይወት በመቀየር ብልጽግና በቤተሰብ ደረጃ እየተረጋገጠ ለመሆኑ ማሣያ ናቸው ብለዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026