የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኮደርስ ስልጠና የተሻለ የዲጂታል እውቀትና ክህሎት እንድናገኝ መልካም አካጣሚ ፈጥሮልናል - ወጣቶች

Jul 7, 2025

IDOPRESS

ጂግጂጋ፤ ሰኔ 27/2017(ኢዜአ)፦ የኮደርስ ስልጠና የተሻለ የዲጂታል እውቀትና ክህሎት እንድናገኝ መልካም አካጣሚ ፈጥሮልናል ሲሉ በጂግጂጋ ከተማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ወጣቶች ተናገሩ።

የሶማሌ ክልል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ በበኩሉ በክረምቱ በእረፍት ላይ የሚገኙ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል።

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከወሰዱ ወጣቶች መካከል ሸርማርኬ ሸኪብ አብዲ፤ የስልጠናው እድል በተለይም ለወጣቶች ጥሩ አጋጣሚ በመሆኑ ጥሩ የዲጂታል እውቀት እና ክህሎት እንድንጨብጥ እያደረገን ነው ብሏል።

ከስልጠናው በቀሰመው እውቀት እና ክህሎት በመታገዝ ዌብሳይት በማበልጸግ የራሱን የንግድ ስራ ለማስተዋወቅ እየተጠቀመበት መሆኑን አንስቶ በነፃ እንዲህ አይነት የትምህርት እድል በማግኘቱ አመስግኗል።

የሚገኘው እውቀት ከሀገርም ባለፈ ዓለም አቀፍ ተፈላጊ የሚያደርግ መሆኑን አንስቶ ሌሎች ወጣቶችም እድሉ እንዳያመልጣቸው መክሯል።

ሌሎች ስልጠናውን ያገኙት ወጣት አብዲሸኩር መሀመድ አብዲ እና ሰከሪዬ አብዲረህማን ዓሌ፤ የኮደርስ ስልጠናው በብዙ መልኩ ጠቃሚ መሆኑን ካገኘነው እውቀትና ክህሎት ተገንዝበናል ብለዋል።

የአሁኔ ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘመን መሆኑን የገለጹት ወጣቶቹ መማር፣ መዘጋጀትና ከወቅቱ ጋር መጓዝ የግድ መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም በተለይም በክረምቱ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ዝግ በመሆናቸው ወጣቶች ጊዜያቸውን የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ እንዲጠቀሙበት አስገንዝበዋል።

የክልሉ የመረጃ ማዕከል አስተዳደር ዳይሬክተር አብዲአዚዝ አብዲላሂ፤ የኢትዮ ኮደርስ ስለጠና እድሜ ሳይገድበው ለሁሉም ዜጎች በነፃ የሚሰጥ የዲጂታል እውቀት በመሆኑ ሁሉም እድሉን እንዲጠቀምበት መክረዋል።

በተለይም ወጣቶች ዘመኑ የሚጠይቀውን ቴክኖሎጂ እውቅት በማዳበር ብቁና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ስልጠናው በእጅጉ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ እስካሁን ከ48ሺህ በላይ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው ሰርተፊኬት የተሰጣቸው መሆኑን ገልጸው በክረምቱ በእረፍት ላይ የሚገኙ ወጣቶች ሁሉ የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026