
ሀዋሳ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል አምራች ኢንተርፕራይዞችን በማጠናከር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ።
ርዕሰ መስተዳድር "የኢንተርፕራይዞች ሚና ለሀገር ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል በሀዋሳ ከተማ የተዘጋጀውን አውደ ርዕይና ባዛር ከፍተዋል።
በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ ያሉ አምራች ኢንተርፕራይዞችን አቅም በማጠናከር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ ይሰራል።

ኢንዱስትሪዎቹ በተሰማሩበት ዘርፍ ስኬታማ እንዲሆኑ የድጋፍና ክትትል ሥራው በትኩረት እንደሚከናወንም አመልክተዋል።
የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ልማት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ከፍያለሁ ከበደ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ በአውደ ርዕይና ባዛሩ ላይ በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ከ220 በላይ አምራች ኢንተርፕራይዞች ይሳተፋሉ።
አምራች ኢንዱስትሪዎቹ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
አውደ ርዕይና ባዛሩ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ ልምድ እንዲለዋወጡና የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።

የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የሚቀርቡበት በመሆኑም በገበያ ዋጋ ማረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አቶ ከፍያለው ተናግረዋል።
በአውደ ርዕይና ባዛሩ መክፈቻ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ክፍት እንደሚሆንም ተገልጿል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026