
ሀዋሳ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል አምራች ኢንተርፕራይዞችን በማጠናከር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ።
ርዕሰ መስተዳድር "የኢንተርፕራይዞች ሚና ለሀገር ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል በሀዋሳ ከተማ የተዘጋጀውን አውደ ርዕይና ባዛር ከፍተዋል።
በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ ያሉ አምራች ኢንተርፕራይዞችን አቅም በማጠናከር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ ይሰራል።

ኢንዱስትሪዎቹ በተሰማሩበት ዘርፍ ስኬታማ እንዲሆኑ የድጋፍና ክትትል ሥራው በትኩረት እንደሚከናወንም አመልክተዋል።
የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ልማት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ከፍያለሁ ከበደ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ በአውደ ርዕይና ባዛሩ ላይ በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ከ220 በላይ አምራች ኢንተርፕራይዞች ይሳተፋሉ።
አምራች ኢንዱስትሪዎቹ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
አውደ ርዕይና ባዛሩ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ ልምድ እንዲለዋወጡና የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።

የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የሚቀርቡበት በመሆኑም በገበያ ዋጋ ማረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አቶ ከፍያለው ተናግረዋል።
በአውደ ርዕይና ባዛሩ መክፈቻ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ክፍት እንደሚሆንም ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026