የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ አምራች ኢንተርፕራይዞችን በማጠናከር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል-አቶ ደስታ ሌዳሞ

Jul 7, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል አምራች ኢንተርፕራይዞችን በማጠናከር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ።

ርዕሰ መስተዳድር "የኢንተርፕራይዞች ሚና ለሀገር ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል በሀዋሳ ከተማ የተዘጋጀውን አውደ ርዕይና ባዛር ከፍተዋል።

በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ ያሉ አምራች ኢንተርፕራይዞችን አቅም በማጠናከር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ ይሰራል።


ኢንዱስትሪዎቹ በተሰማሩበት ዘርፍ ስኬታማ እንዲሆኑ የድጋፍና ክትትል ሥራው በትኩረት እንደሚከናወንም አመልክተዋል።

የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ልማት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ከፍያለሁ ከበደ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ በአውደ ርዕይና ባዛሩ ላይ በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ከ220 በላይ አምራች ኢንተርፕራይዞች ይሳተፋሉ።

አምራች ኢንዱስትሪዎቹ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

አውደ ርዕይና ባዛሩ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ ልምድ እንዲለዋወጡና የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።


የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የሚቀርቡበት በመሆኑም በገበያ ዋጋ ማረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አቶ ከፍያለው ተናግረዋል።

በአውደ ርዕይና ባዛሩ መክፈቻ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ክፍት እንደሚሆንም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026