የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ወደ ፖርቶ የተጀመረው በረራ የፖርቹጋል እና ኢትዮጵያን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክር ነው

Jul 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦ወደ ፖርቶ የተጀመረው በረራ የፖርቹጋልና ኢትዮጵያን ግንኙነት የሚያጠናክርና ለአገራቱ የቱሪዝም እድገት አስተዋፅኦ የሚያበረክት መሆኑን በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባሳደር ልዊሳ ፋራጎሶ ገለፁ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሣምንት አራት ጊዜ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ ከተማ አዲስ በረራ መጀመሩ ይታወሳል።


በረራው ሁለቱ አገራትን በቱሪዝም፤ንግድና ኢንቨስትመንት በማስተሳሰር ወዳጅነትታቸውን እንዲያጠናክሩ ትልቅ ሚና እንዳለው ታምኖበታል።

አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ የጀመረውን በረራን አስመልክቶም ትናንት ምሽት በፖርቶ ከተማ የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብር ተከናውኗል።

በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባሳደር ልዊሳ ፋራጎሶ በኢትዮጵያ በርካታ የልማት የትብብር እድሎች እንዳሉ ተናግረዋል።

በትራንስፖርት አለመተሳሰር ይህን እድል በመጠቀም ረገድ ውስንነት ፈጥሮ መቆየቱን አንስተው፤ አየር መንገዱ ወደ ፖርቹጋል የጀመረው በረራም ችግሩን ለማቃለል ዓይነተኛ ሚና እንዳለው አብራርተዋል።

የፖርቶ ከተማ ቱሪዝም ቦርድ ፕሬዝዳንት ፔድሮ ማርቲንስ በበኩላቸው፣ የአየር መንገዱ ወደፖርቶ በረራ መጀመር የሁለቱን አገራት የቱሪዝም መዳረሻዎች ለማስተዋወቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ተናግረዋል።

በፖርቹጋልና ኢትዮጵያ በርካታ የቱሪዝም ስፍራዎች እንዳሉ አንስተው፤ አየር መንገዱ የጀመረው በረራም እነዚህን ስፍራዎች ወደ ልማት ለመቀየር ትልቅ አቅም መሆኑን አብራርተዋል።


ፖርቹጋላዊያን ቱሪስቶች የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፈጠረው እድል ኢትዮጵያን እንዲጎበኙም ጥሪ አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ ሆሊደይና ዲጂታል ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ሃይለመለኮት ማሞ በበኩላቸው፤ ወደፖርቶ የተጀመረው በረራ አየር መንገዱ ከአውሮፓ ጋር ያለው ጠንካራ የትራንስፖርት ትስስር ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።


አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር እያከናወናቸው ያሉ ስራዎች አካል ስለመሆኑም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026