የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በጋምቤላ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 223 ባለሃብቶች ፈቃድ ወስደዋል - ኮሚሽኑ

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 223 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።

በግብርናው ዘርፍ ፍቃድ የወሰዱ 38 ባለሃብቶች በሙሉ የእርሻ መሬት ተረክበው ወደ ስራ መግባታቸውም ተገልጿል።

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለማስተዋወቅ በተሰሩ ስራዎችና በአካባቢው የሰፈነው ሰላም የአልሚ ባለሃብቶች ፍሰት እንዲጨምር አስችሏል።

በዚህም በ2017 በጀት ዓመት ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 223 ባለሃብቶች ፈቃድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል።

ባለሃብቶቹ ፈቃዱን የወሰዱት በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት የኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሰማራት መሆኑንም ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት ፈቃድ ከወሰዱት ባለሃብቶች መካከል 123ቱ መሬት ተረክበው ወደ ልማት መግባታቸውንም ገልፀዋል።

ፍቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ ሲገቡ ከ11ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።

በግብርናው ዘርፍ ብቻ ፈቃድ ከወሰዱ ባለሃብቶች 38ቱ የእርሻ መሬት ተረክበው ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።


በክልሉ ጋምቤላ ወረዳ በግብርና ኢንቨስትመንት ከተሰማሩ ባለሀብቶች መካከል አቶ ኡሞድ ኡገር በሰጡት አስተያየት ለግብርና ልማት የተረከቡትን የእርሻ መሬት ማልማታቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የሚያደርግላቸው ክትትልና ሙያዊ እገዛ በስራችው ውጤታማ እንዲሆኑ ማገዙን ጠቁመዋል።


በክልሉ ለግብርናው ኢንቨስትመንት ዘርፍ ምቹና ተስማሚ ስነ-ምህዳር በመኖሩ የተረከቡትን የእርሻ መሬት ማልማታቸውን የገለጹት ደግሞ በክልሉ አቦቦ ወረዳ በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ ፍቅሬ ገብረ መድህን ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026