
ጋምቤላ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 223 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
በግብርናው ዘርፍ ፍቃድ የወሰዱ 38 ባለሃብቶች በሙሉ የእርሻ መሬት ተረክበው ወደ ስራ መግባታቸውም ተገልጿል።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለማስተዋወቅ በተሰሩ ስራዎችና በአካባቢው የሰፈነው ሰላም የአልሚ ባለሃብቶች ፍሰት እንዲጨምር አስችሏል።
በዚህም በ2017 በጀት ዓመት ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 223 ባለሃብቶች ፈቃድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል።
ባለሃብቶቹ ፈቃዱን የወሰዱት በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት የኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሰማራት መሆኑንም ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት ፈቃድ ከወሰዱት ባለሃብቶች መካከል 123ቱ መሬት ተረክበው ወደ ልማት መግባታቸውንም ገልፀዋል።
ፍቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ ሲገቡ ከ11ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
በግብርናው ዘርፍ ብቻ ፈቃድ ከወሰዱ ባለሃብቶች 38ቱ የእርሻ መሬት ተረክበው ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ ጋምቤላ ወረዳ በግብርና ኢንቨስትመንት ከተሰማሩ ባለሀብቶች መካከል አቶ ኡሞድ ኡገር በሰጡት አስተያየት ለግብርና ልማት የተረከቡትን የእርሻ መሬት ማልማታቸውን ገልጸዋል።
የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የሚያደርግላቸው ክትትልና ሙያዊ እገዛ በስራችው ውጤታማ እንዲሆኑ ማገዙን ጠቁመዋል።

በክልሉ ለግብርናው ኢንቨስትመንት ዘርፍ ምቹና ተስማሚ ስነ-ምህዳር በመኖሩ የተረከቡትን የእርሻ መሬት ማልማታቸውን የገለጹት ደግሞ በክልሉ አቦቦ ወረዳ በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ ፍቅሬ ገብረ መድህን ናቸው።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026