የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል የፈጠሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን እየተገበረች ነው

Jul 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም አካባቢ እያከናወነቻቸው ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል እየፈጠሩ መሆኑን መገንዘባቸውን የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ተሳታፊዎች ገለጹ።

በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው ሦስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም በአህጉሪቱ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም ለአፍሪካውያን ወጣቶች የሥራ እድል ለመፍጠር ትብብርን የሚያጎለብት እንደሆነ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

ኡጋንዳዊው ተሳታፊ ናምጎ ጆብ እንደገለጸው፤ ፎረሙ በአፍሪካ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም በሥራ እድል ፈጠራ የተያዙ እቅዶችን በትብብር መተግበር ለአህጉሪቷ ወጣቶች ተስፋ የሚሰጥ ነው።

ይህም አፍሪካውያን ወጣቶች በአገራቸው ሰርተው የመበልጸግ ርዕያቸውን እውን በማድረግ ከስደት እንደሚታደጋቸው ገልጿል።

ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አዲስ አበባ የመጣው እ.ኤ.አ በ2023 እንደነበር በማስታወስ፤ አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ሲመጣ የአዲስ አበባ የመሰረተ ልማት መስፋፋትና የከተማዋ እድገት እንዳስገረመውም ጠቅሷል።

የአዲስ አበባ ዘመናዊ መሰረተ ልማት፣ የከተማ ውበት፣ የጎዳናዎች ስፋትና ጽዳት "በአፍሪካ የአውሮፓ ከተማ ውስጥ እንዳለሁ ተሰምቶኛል" ሲል የከተማዋን ዕድገት አድንቋል።

በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጥሩ መሆኑን መገንዘቡን በማንሳት፥ ኢትዮጵያ በብሩህ ተስፋ ጉዞ ላይ ናት ብለዋል።

በኮሜሳ የሴት ነጋዴዎች ማህበር ፌዴሬሽን የቦርድ ሊቀ መንበር ሞሪን ሶቦይ ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡበት ወቅት የሚያገኙት አዳዲስ ለውጥ ሀገሪቱ በፈጣን እድገት ላይ መሆኗን የሚያመላክት እንደሆነ ገልጸዋል።


ሌሎች የአፍሪካ አገራትም ከኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ልምድ ሊወስዱ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

አዲስ አበባ በከተማ ውበት፣ እድገትና ጽዱ አካባቢን በመፍጠር እያሳየች ያለው ለውጥም ለመኖሪያ ምቹ ያደርጋታል ነው ያሉት።

በኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የስራ ድርጅት ዋና የቴክኒክ አማካሪ አንቶኒ አይንታ ኢትዮጵያ ለራሷ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት አገሮችም አቅም መሆን የሚችል ብቁ የሰው ሃይል አላት ብለዋል።


አህጉሪቱን በንግድና አገልግሎት ለማስተሳሰር ከተያዘው ራዕይ ጎን ለጎን በሰለጠነ የሰው ሃይል የወጣቶችን እውቀት በመጠቀም በስራ ፈጠራ ማስተሳሰር እንደሚቻል ጨምረዋል።

ሦስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም የግብርና እሴት ሰንሰለት፣ ዲጂታላይዜሽንና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ አስተማማኝ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር ላይ ምክክር በማድረግ ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026