
ነቀምቴ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦በምስራቅ ወለጋ ዞን በሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን መቻሉን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ወጋሪ ነገራ ገለጹ።
በዞኑ ሲቡ ስሬ ወረዳ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማዕከል አድርገው የተገነቡ 41 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።
የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳደሪ አቶ ወጋሪ ነገራ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በዞኑ የሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በስፋት ለማከናወን እድል ፈጥሯል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት እየበቁ መሆኑን ገልጸዋል።
በዞኑ ሲቡ ሲሬ ወረዳ በ435 ሚሊዮን ብር የተገነቡ 41 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችም የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ተናግረዋል።
ለአገልግሎት እየበቁ ያሉ የመሰረተ ልማት ተቋማት የትምህርት፣ የጤና፣ መሰረተ ልማት እና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል።
በዞኑ ሁሉንም ነዋሪዎች ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች እንደሚጠናከሩ ገልጸው፣ የዞኑ ህዝብም የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።
የሲቡ ስሬ ወረዳ አስተዳደሪ አቶ ጨነቀ ቡሻ በበኩላቸው ለአገልግሎት የበቁ የመሰረተ ልማት ተቋማት በመንግሥት በጀትና በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡ ናቸው ብለዋል።

የፕሮጀክቶቹ ለአገልግሎት መብቃት ለዓመታት ሲነሱ ለነበሩ የህብረተሰብ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይም የወረዳውን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።

በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶቹ ምርቃት ላይ የተገኙት የወረዳው ነዋሪዎችም የልማት ሥራው ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026