የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምስራቅ ወለጋ ዞን በሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን ተችሏል-የዞኑ አስተዳደር

Jul 10, 2025

IDOPRESS

ነቀምቴ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦በምስራቅ ወለጋ ዞን በሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን መቻሉን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ወጋሪ ነገራ ገለጹ።

በዞኑ ሲቡ ስሬ ወረዳ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማዕከል አድርገው የተገነቡ 41 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳደሪ አቶ ወጋሪ ነገራ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በዞኑ የሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በስፋት ለማከናወን እድል ፈጥሯል።


በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት እየበቁ መሆኑን ገልጸዋል።

በዞኑ ሲቡ ሲሬ ወረዳ በ435 ሚሊዮን ብር የተገነቡ 41 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችም የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ተናግረዋል።

ለአገልግሎት እየበቁ ያሉ የመሰረተ ልማት ተቋማት የትምህርት፣ የጤና፣ መሰረተ ልማት እና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል።

በዞኑ ሁሉንም ነዋሪዎች ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች እንደሚጠናከሩ ገልጸው፣ የዞኑ ህዝብም የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።

‎የሲቡ ስሬ ወረዳ አስተዳደሪ አቶ ጨነቀ ቡሻ በበኩላቸው ለአገልግሎት የበቁ የመሰረተ ልማት ተቋማት በመንግሥት በጀትና በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡ ናቸው ብለዋል።


የፕሮጀክቶቹ ለአገልግሎት መብቃት ለዓመታት ሲነሱ ለነበሩ የህብረተሰብ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይም የወረዳውን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።


በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶቹ ምርቃት ላይ የተገኙት የወረዳው ነዋሪዎችም የልማት ሥራው ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026