
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገሮች በልማት በሚተሳሰሩባቸው ምቹ ሁኔታዎች ላይ በትኩረት እየሰራች መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለፁ።
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሲካሔድ የቆየው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም የማጠናቀቂያ መርኃ ግብር እየተካሄደ ነው።

አቶ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገሮች በልማት በሚተሳሰሩባቸው ምቹ ሁኔታዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ትገኛለች።
በተለይም የአህጉሪቱ ወጣቶች በልማት፣ በኢኮኖሚና በስራ እድል ፈጠራ የሚቀናጁበትን ሁኔታ ማመቻቸት አንዱና ዋነኛው መሆኑን ገልጸዋል።
ላለፉት ሦስት ቀናት የተካሔደው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም የዚሁ አካል መሆኑንም ገልጸው በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ሀገሮች በኢኮኖሚ፣ በልማትና መሰል ተግባራት ላይ ያላቸው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ይህም የአህጉሪቱን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት ጥቅም ላይ ለማዋል ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በለውጡ ዓመታት ያካሄደችው ሀገራዊ ሪፎርም እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን ወጥ በሆነ መልኩ ማከናወን እንዳስቻላት አስታውቀዋል።
በተለይም አምስት የኢኮኖሚ ልማት ምሰሶዎችን በመለየት እያከናወነች ባለው ተግባር አበረታች ውጤት መመዝገቡን አብራርተዋል።
የአህጉሪቱን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ አካታች የኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሆኑንም ነው አቶ አደም ፋራህ የጠቆሙት።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026