
ሚዛን አማን፣ ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)፡-በአካባቢያቸው በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠቃሚ በመሆናቸው የልማት ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የቴፒ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
በከተማዋ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሳይሰጥ የቆየው የቴፒ አነስተኛ አውሮፕላን ማረፊያ ከ30 ዓመታት በኋላ ዳግም ወደ አገልግሎት መግባት የአካባቢውን ጸጋዎች በአግባቡ ለመጠቀም እንደሚያስችልም ተናግረዋል።
ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ዓለሙ ጣማ እንደገለጹት መንግስት በየአካባቢው ያሉ ሀብቶችን በማልማት ለህዝብ ጥቅም ለማዋል እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው።

ለዚህም የቴፒ አውሮፕላን ማረፊያን ለአብነት የጠቀሱት አቶ ዓለሙ፣ ከ30 ዓመታት በኋላ ዳግም አገልግሎት በመጀመሩ መደሰታቸውን ገልጸዋል።
አቶ ሰይድ ጦይብ በበኩላቸው ሰሞኑን በአካባቢው የተመረቁ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠቃሚነታቸውን ያረጋገጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል ድልድይ እና የቡና ጥራት ምርምርና ሰርቲፊኬሽን ማዕከልን በማሳያነት ጠቅሰው፣ ለአካባቢው የልማት ሥራዎች የሚያደርጉትን አስተዋጾ እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል።

ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በአካባቢያቸው በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን የተናገሩት ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ባህሩ ወልደጊዮርጊስ ናቸው።
ለዘመናት ሲነሳ የነበረው የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄያቸው ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ በሦስት አቅጣጫ ወደከተማዋ እየተገነቡ ያሉ መንገዶች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴያቸውን እንደሚያፋጥነው ተናግረዋል።

የመሠረተ ልማት መስፋፋት ሰርቶ የመለወጥ ዕድልን የሚያሰፋና ለሥራ የሚያነሳሳ መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት ታምራት ታከለ ሌላው የከተማው ነዋሪ ነው።
አሁን ላይ በአካባቢው ያለው የልማት እንቅስቃሴ የተሻለና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ተናግሮ፣ ለአካባቢው ልማት መፋጠን የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጿል።

በሸካ ዞን ግንባታቸው የተጠናቀቁ አምስት መሠረተ ልማቶች ሰሞኑን የክልሉና የፌደራል ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃታቸው የሚታወስ ነው።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026