የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ዳያስፖራውን ተጠቃሚ የሚያደርግ የአሰራር ማሻሻያ እየተደረገ ነው

Jul 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2017(ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት ማሻሻያ ዳያስፖራውን ተጠቃሚ የሚያደርግ የአሰራር ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ ለኢዜአ እንዳሉት የዳያስፖራ ፖሊሲ ስራ ላይ ከዋለ አስራ ሶስት አመታትን አስቆጥሯል።

በእነዚህ አመታትም በምጣኔ ሃብት፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች በተደረጉ ማሻሻያዎች በርካታ ለውጦች መመዝገባቸውን አንስተዋል።

በተለይም ባለፉት ሰባት አመታት በውጭና በአገር ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚያደርግ ምጣኔ ሃብት ለመገንባት የተለያዩ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን አንስተዋል።

በአሁኑ ወቅትም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚ የሚሆኑበት የአሰራር ማሻሻያ በሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

በተመሳሳይ በቅርቡ ተግባራዊ መደረግ የጀመረው ሁለተኛው የአገር በቀል ምጣኔ ሃብት መርሃ ግብርን ታሳቢ ያደረገ ማሻሻያ ማስፈለጉን በማንሳት።

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያም በተለያየ የአለም አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚ የሚሆኑበት መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ካሉበት ሆነው ገንዘባቸውን በሚፈልጉበት የኢንቨስትመንት ዘርፍ ማዋል የሚያስችል አሰራር በመሆኑ ፖሊሲው በዚሁ አግባብ የተቃኘ እንደሆነ አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ከሚገኙ የአፍሪካ አገራት አንዷ በመሆኗ በዚህ ወቅት የሚደረግ ኢንቨስትመንት አዋጭ እንደሆነም አምባሳደር ፍጹም ተናግረዋል።

በመሆኑም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እድሉን በመጠቀም የኢንቨስትመንት ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዲያስፖራው አገሩንና እራሱን ተጠቃሚ እንዲያደርግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም አምባሳደር ፍጹም አረጋ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026