
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2017(ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት ማሻሻያ ዳያስፖራውን ተጠቃሚ የሚያደርግ የአሰራር ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ ለኢዜአ እንዳሉት የዳያስፖራ ፖሊሲ ስራ ላይ ከዋለ አስራ ሶስት አመታትን አስቆጥሯል።
በእነዚህ አመታትም በምጣኔ ሃብት፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች በተደረጉ ማሻሻያዎች በርካታ ለውጦች መመዝገባቸውን አንስተዋል።
በተለይም ባለፉት ሰባት አመታት በውጭና በአገር ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚያደርግ ምጣኔ ሃብት ለመገንባት የተለያዩ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን አንስተዋል።
በአሁኑ ወቅትም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚ የሚሆኑበት የአሰራር ማሻሻያ በሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
በተመሳሳይ በቅርቡ ተግባራዊ መደረግ የጀመረው ሁለተኛው የአገር በቀል ምጣኔ ሃብት መርሃ ግብርን ታሳቢ ያደረገ ማሻሻያ ማስፈለጉን በማንሳት።
የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያም በተለያየ የአለም አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚ የሚሆኑበት መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ካሉበት ሆነው ገንዘባቸውን በሚፈልጉበት የኢንቨስትመንት ዘርፍ ማዋል የሚያስችል አሰራር በመሆኑ ፖሊሲው በዚሁ አግባብ የተቃኘ እንደሆነ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ከሚገኙ የአፍሪካ አገራት አንዷ በመሆኗ በዚህ ወቅት የሚደረግ ኢንቨስትመንት አዋጭ እንደሆነም አምባሳደር ፍጹም ተናግረዋል።
በመሆኑም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እድሉን በመጠቀም የኢንቨስትመንት ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዲያስፖራው አገሩንና እራሱን ተጠቃሚ እንዲያደርግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም አምባሳደር ፍጹም አረጋ ተናግረዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026