
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፦የኮሪደር ልማቱ ከተጎሳቆለ አካባቢ በማላቀቅ የተሻለ ህይወት ለመምራት እንዳስቻላቸው የመዲናዋ የመልሶ ማልማት ተነሺዎች ገለጹ።
አዲስ አበባ ከለውጡ ወዲህ ስሟን እና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን የሚመጥን ገጽታ ለማላበስ እና የነዋሪዎቿን ህይወት ለማሻሻል በርካታ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን በዚህም የሚታዩ ለውጦች ተመዝግበዋል።
በዚህም መዲናዋ ውብ፣ ጽዱ እና የዓለም አቀፍ ቱሪስቶች የስህበት ማዕከል እየሆነች መጥታለች፡፡
በተለይ በሁለት ምዕራፍ ተከፋፍሎ የተከናወነው እና በመከናወን ላይ ያለው የኮሪደር ልማት ለከተማዋ ገጽታ እና ለነዋሪዎች ህይወት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡
ኢዜአ በኮሪደር ልማቱ ከከተማዋ የተለያዩ ሰፈሮች ተነስተው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በሚገኘው አዲስ እና ደረጃውን የጠበቀ የመኖሪያ አካባቢ ህይወት መምራት የጀመሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን አነጋግሯል።
ከፒያሳ በመልሶ ማልማት የተነሱት አልማዝ ዳምጠው፤ ቀደም ሲል በተጎሳቆለና ለህይወት ፈታኝ በሆነ አኗኗር ውስጥ ያሳልፉ እንደነበር አውስተዋል።
የኮሪደር ልማቱ መምጣቱን ተከትሎ መኖሪያ አካባቢያቸው ወደ መልሶ ማልማት ሲገባ፥ እነሱም ምቹ ካልሆነው አሮጌ አካባቢ ወጥተው ደረጃውን ወደጠበቀ የመኖሪያ መንደር መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡
ልማቱ ከነበርንበት ደሳሳ ጎጆ በመውጣት በተሻለ ሁኔታ እንድንኖርና ልጆቻችን በምቹ ትምህርት ቤቶች እንዲማሩ ያስቻለ ነው ብለዋል፡፡
ከቄራ በመልሶ ማልማት የተነሱት ሙና ሸሪፍ በበኩላቸው፤ አሁን ያሉበት አካባቢ በውሃ፣ በጤና፣ በመብራትና ሌሎች አቅርቦቶች ከበፊቱ እጅግ የተሻለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ትምህርት ቤቶቹ የስፖርት ማዘውተሪያ ያላቸው፣ የመመገቢያ ማዕከል የተገነባላቸው እና ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውንም አንስተዋል፡፡
የተገነቡ መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃን ያሟሉ በመሆናቸው መንግስትን እናመሰግናለን ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ሰናይት ገብሩ ናቸው፡፡
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026