
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዓላማን በመደገፍ ለትግበራው ያሳየችው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው ሲሉ በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሴክሬተሪያት የማስተባበሪያና ፕሮግራም ዳይሬክተር ሶቴሲ ማኮንግ(ዶ/ር) ገለጹ።
ዳይሬክተሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቷን የንግድ ልውውጥ ለማጠናከር እና ለስራ እድል ፈጠራ ጉልህ ሚና የሚጫወት ነው።
በንግድ ቀጣናው በሚደረግ የንግድ ልውውጥ በትራንስፖርት፣ ንግድ፣ አገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች የሚኖረው ሰንሰለት ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ የአህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናውን ዓላማ በመደገፍ ለትግበራው ያሳየችው ቁርጠኝነትና እያደረገች ያለው ዝግጅት የሚደነቅ እንደሆነ ተናግረዋል።
ነጻ የንግድ ቀጣናው ያመጣውን ዕድል ለመጠቀም ነጋዴዎችና ኢንቨስተሮች ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።
የአፍሪካ አገራት በአህጉሪቱ ያለውን የንግድ ልውውጥ ከቀረጥ ነጻ ለማድረግ ያደረጉት ስምምነት ለነጋዴዎችና አምራቾች ምርትን ለማሳደግና ንግድን ለማስፋት ትልቅ ዕድል ይዞ መምጣቱን ነው የገለጹት።
እ.ኤ.አ በ2050 ከአፍሪካ ህዝብ ቁጥር ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው ወጣት እንደሚሆን መተንበዩን በማስታወስ የስራ እድል ፈጠራ እድሎችን ማስፋት ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው እንደሆነም ነው የተናገሩት።
በዚህ ረገድ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በስራ እድል ፈጠራ ያለውን እድል አሟጦ ለመጠቀም ከወዲሁ ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሴክሬተሪያት ትግበራውን ለማሳለጥ ሃገራትን በማስተባበር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026