የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ ለነጻ የንግድ ቀጣና ትግበራ ያሳየችው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው

Jul 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዓላማን በመደገፍ ለትግበራው ያሳየችው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው ሲሉ በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሴክሬተሪያት የማስተባበሪያና ፕሮግራም ዳይሬክተር ሶቴሲ ማኮንግ(ዶ/ር) ገለጹ።

ዳይሬክተሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቷን የንግድ ልውውጥ ለማጠናከር እና ለስራ እድል ፈጠራ ጉልህ ሚና የሚጫወት ነው።

በንግድ ቀጣናው በሚደረግ የንግድ ልውውጥ በትራንስፖርት፣ ንግድ፣ አገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች የሚኖረው ሰንሰለት ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የአህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናውን ዓላማ በመደገፍ ለትግበራው ያሳየችው ቁርጠኝነትና እያደረገች ያለው ዝግጅት የሚደነቅ እንደሆነ ተናግረዋል።

ነጻ የንግድ ቀጣናው ያመጣውን ዕድል ለመጠቀም ነጋዴዎችና ኢንቨስተሮች ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።

የአፍሪካ አገራት በአህጉሪቱ ያለውን የንግድ ልውውጥ ከቀረጥ ነጻ ለማድረግ ያደረጉት ስምምነት ለነጋዴዎችና አምራቾች ምርትን ለማሳደግና ንግድን ለማስፋት ትልቅ ዕድል ይዞ መምጣቱን ነው የገለጹት።

እ.ኤ.አ በ2050 ከአፍሪካ ህዝብ ቁጥር ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው ወጣት እንደሚሆን መተንበዩን በማስታወስ የስራ እድል ፈጠራ እድሎችን ማስፋት ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው እንደሆነም ነው የተናገሩት።

በዚህ ረገድ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በስራ እድል ፈጠራ ያለውን እድል አሟጦ ለመጠቀም ከወዲሁ ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሴክሬተሪያት ትግበራውን ለማሳለጥ ሃገራትን በማስተባበር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026