🔇Unmute
አዳማ ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ)፡-በምዕራብ አርሲ ዞን በ97 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ቦሎቄ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለፀ።
የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አብዱላሂ ቤከን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት በዞኑ ቆላማ አካባቢዎች ቦሎቄን ጨምሮ የጥራጥሬ ሰብሎች ልማት በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።
በተለይም በሻሸመኔ፣ አርሲ ነገሌ፣ ቆሬ፣ ሻላና ሄበን አርሲ ወረዳዎች ላይ ለወጪ ንግድ የሚሆን ቦሎቄ በስፋት እየለማ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
አርሶ አደሩ በራሱ ማሳ ላይ ከሚያለማው ቦሎቄ ባሻገር ከባለሃብቶች ጋር የውል እርሻ በማስገባትና አርሶ አደሮችን በኩታ ገጠም በማደራጀት እያለማ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በገቡት ውልና ትብብር መሰረት የቦሎቄ ምርጥ ዘር፣ የአፈር ማዳበሪያ፣ ቴክኖሎጂና የሜካናይዜሽን አገልግሎትን ጨምሮ የተሟላ የግብርና ኤክስቴንሽን ድጋፍ ለአርሶ አደሮቹ እየተሰጠ ቦሎቄን በተሻለ ደረጃ እያለሙ ይገኛሉ ብለዋል።
በአጠቃላይ በዞኑ በቦሎቄ ከሚለማው 97 ሺህ ሄክታር መሬት ውስጥ 57 ሺህ ሄክታሩ በውል እርሻ እንዲታቀፍ ተደርጎ ሰብሉ በተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ኃላፊው ተናግረዋል።
በቆላማ የዞኑ ወረዳዎች አርሶ አደሩ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ እንዲያመርት ድንችን ጨምሮ የአፈር ለምነትን የሚጠብቁ የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎች እየለሙ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በዚህም አርሶ አደሩ ምርታማነቱ እንዲጨምርና አማራጭ የገቢ ምንጭ እንዲያገኝ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በቦሎቄ ልማት ከተሸፈነው መሬትም 2 ሚሊዮን ኩንታል ምርት የሚጠበቅ መሆኑንም ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል።
በዞኑ አርሶ አደሮች በግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ አቅምን ማሳደግና ተኪ ምርቶችን ማምረት ላይ ትኩረት በማድረግ እየሰሩ እንደሚገኙም ተናግረዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026