የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በግብርና ማቀነባበር ዘርፍ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በሊዝ ፋይናንስ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር እንሰራለን -የኢትዮጵያ ልማት ባንክ

Sep 30, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ)፦ በግብርና ማቀነባበር ዘርፍ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በሊዝ ፋይናንስ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ገለጹ።

ሊዝ ፋይናንስ ባንኩ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የካፒታል ዕቃዎችን ገዝቶ ለኪራይ የሚያቀርበው አገልግሎት ነው።

በዚህም ባንኩ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድንና በሌሎችም ዘርፎች ለተሰማሩ አምራቾች የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎትን እየሰጠ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፤ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በቂ መሰረተ ልማት መገንባቱን አንስተዋል።

ይሁንና መሰረተ ልማታቸው በተሟላ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ተወዳዳሪ ባለሃብቶች በሚፈለገው ልክ አለመግባታቸውንም ነው ያነሱት።


ይህን ችግር ለመፍታት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚያቀርበውን የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት የበለጠ ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በዚህም በተለይ በግብርና ማቀነባበር የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በሊዝ ፋይናንስ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል።

የግብርና ዘርፉን ምርትና ምርታማነት ማሳደግና የምርት ብክነትን መቀነስ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ በቂ ግብዓት ማቅረብ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።

በግብርና ማቀነባበር ዘርፍ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የበለጠ ውጤታማ የሚሆኑበትን የሊዝ ፋይናንሰ አቅርቦት ማሳደግ ላይ ጥናትና ምርምር የማድረግ ተግባር የሁሉም ባንኮች ድርሻ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት።

ከዚህ አኳያ ባንኩ በሊዝ ፋይናንስ ያለውን የካበተ ልምድ በመጠቀም ከሌሎች ባንኮች ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.