🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ)፦ በግብርና ማቀነባበር ዘርፍ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በሊዝ ፋይናንስ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሊዝ ፋይናንስ ባንኩ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የካፒታል ዕቃዎችን ገዝቶ ለኪራይ የሚያቀርበው አገልግሎት ነው።
በዚህም ባንኩ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድንና በሌሎችም ዘርፎች ለተሰማሩ አምራቾች የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎትን እየሰጠ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፤ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በቂ መሰረተ ልማት መገንባቱን አንስተዋል።
ይሁንና መሰረተ ልማታቸው በተሟላ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ተወዳዳሪ ባለሃብቶች በሚፈለገው ልክ አለመግባታቸውንም ነው ያነሱት።

ይህን ችግር ለመፍታት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚያቀርበውን የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት የበለጠ ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በዚህም በተለይ በግብርና ማቀነባበር የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በሊዝ ፋይናንስ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል።
የግብርና ዘርፉን ምርትና ምርታማነት ማሳደግና የምርት ብክነትን መቀነስ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ በቂ ግብዓት ማቅረብ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።
በግብርና ማቀነባበር ዘርፍ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የበለጠ ውጤታማ የሚሆኑበትን የሊዝ ፋይናንሰ አቅርቦት ማሳደግ ላይ ጥናትና ምርምር የማድረግ ተግባር የሁሉም ባንኮች ድርሻ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት።
ከዚህ አኳያ ባንኩ በሊዝ ፋይናንስ ያለውን የካበተ ልምድ በመጠቀም ከሌሎች ባንኮች ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026