የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የማዳበሪያ ፋብሪካ በሀገር ውስጥ መገንባቱ ለግብርናው ሴክተር ማርሽ ቀያሪ ፕሮጀክት ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ በሀገር ውስጥ ለመገንባት መወሰኑና ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ለግብርናው ሴክተር ማርሽ ቀያሪ ተግባር መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ከዳንጎቴ ግሩፕ ጋር በመተባበር የሚገነባው የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጣቸው ይታወቃል።

በዚሁ ወቅትም የማዳበሪያ ፋብሪካው ከካሉብ የጋዝ ስፍራ በማውጣት እና 108 ኪሎሜትር የማጓጓዣ ቱቦ በመጠቀም በዓመት 3 ሚሊየን ቶን ማዳበሪያ አምርቶ ያቀርባል ማለታቸው ይታወሳል።

ይህን አስመልክቶም በግብርና ሚኒስቴር የግብዓት አቅርቦት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ተስፋ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ፕሮጀክቱ በሀገራችን የመጀመሪያ በመሆኑ እና በዘርፉ የሚስተዋሉ ዕክሎችን በማረቅ ረገድ የጎላ ሚና እንዳለው አንስተዋል።


እንደ ሀገር ዘርፈ-ብዙ ጥቅም እንዳለው ጠቁመው፤ በተለይም ለግብርናው ዘርፍ ማርሽ ቀያሪ ትልቅ ተግባር ስለመሆኑ በአጽንኦት ገልጸዋል።

ቀዳሚው የግብርና ዘርፍ ተልዕኮ ምርትና ምርታማነትን መጨመር መሆኑን እና ለዚህ ደግሞ ግብዓት ወሳን መሆኑን አንስተዋል።

ተልዕኳችንን በሚፈለገው ልክ ለማሳካት የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ በሀገር ውስጥ መገንባቱ ቁልፍ ጉዳይ ነው ሲሉ በአጽንኦት ገልጸዋል።

የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካው በሀገር ውስጥ መገንባቱ የሚጨምራቸው በጎ ነገሮች እና የሚቀንሳቸው ጫናዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።

በዚህም መሠረት፤ በምንፈልግበት ጊዜ፣ የምንፈልገውን መጠን እና ዓይነት አፈር ማዳበሪያ ለማግኘት ያስችላል ብለዋል።

ለአብነትም ከዓለም ሀገራት ጋር ተወዳድረን የምንፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ ዓይነት ለማግኘት ተቸግረን እናውቃለን ሲሉም አስታውሰዋል።

ከዚህ አኳያ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ በሀገር ውስጥ መገንባቱ ከፍተኛ ሚና እንዳለው በአጽንኦት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.