🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያውያን ጀግንነታቸውን ሀገር በማልማትና በመቀየር ሊያሳዩ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከፌዴራል እና ክልል አመራሮች ጋር የገጠር ኮሪደር ስራዎች ላይ ውይይት አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዚህ ዘመን የኢትዮጵያውያን ጀግንነት ሀገርን በማልማትና በመቀየር እንዲሁም ህዝብን መቀየር ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለም ሀገር እና መሬት ይዘን ልንለምን አይገባም፤ የልመና ታሪካችንና የዜጎችን ህይወት መለወጥ የምንችለው ተግቶ በመስራት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን ለበጎ አላማ በመደመር በሀገር ደረጃ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት መስራት እንዳለባቸውም ነው ያመላከቱት።
ቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ነገር እንዲረከብ ዛሬ ላይ ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

ለማህበረሰብ የሚታይ እና የሚጨበጥ ስራ ለመስራት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
ውድድር በልማት እና በስራ ሊሆን ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ክልሎች ባለቸው አቅም በመስራት የዜጎችን ህይወት ከቀየሩ ያለ ምንም ጥርጥር የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት እንደሚቻል ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያውን አንችልም የሚለውን ሀሳብ እና አመለካከት መስበር ይገባናል፤ ኢትዮጵያውያን መቻላችንን ድሮም አሳይተናል አሁንም ችለን ማሳየት አለብን ብለዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026