🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያውያን ጀግንነታቸውን ሀገር በማልማትና በመቀየር ሊያሳዩ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከፌዴራል እና ክልል አመራሮች ጋር የገጠር ኮሪደር ስራዎች ላይ ውይይት አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዚህ ዘመን የኢትዮጵያውያን ጀግንነት ሀገርን በማልማትና በመቀየር እንዲሁም ህዝብን መቀየር ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለም ሀገር እና መሬት ይዘን ልንለምን አይገባም፤ የልመና ታሪካችንና የዜጎችን ህይወት መለወጥ የምንችለው ተግቶ በመስራት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን ለበጎ አላማ በመደመር በሀገር ደረጃ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት መስራት እንዳለባቸውም ነው ያመላከቱት።
ቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ነገር እንዲረከብ ዛሬ ላይ ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

ለማህበረሰብ የሚታይ እና የሚጨበጥ ስራ ለመስራት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
ውድድር በልማት እና በስራ ሊሆን ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ክልሎች ባለቸው አቅም በመስራት የዜጎችን ህይወት ከቀየሩ ያለ ምንም ጥርጥር የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት እንደሚቻል ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያውን አንችልም የሚለውን ሀሳብ እና አመለካከት መስበር ይገባናል፤ ኢትዮጵያውያን መቻላችንን ድሮም አሳይተናል አሁንም ችለን ማሳየት አለብን ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026