የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ ኢኖቬተሮች እና ስራ ፈጣሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኘው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ሁነት በዱባይ እየተካሄደ ነው

Oct 14, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- 45ኛው የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) ዛሬ በዱባይ ዓለም አቀፍ የንግድ ማዕከል ተጀምሯል።

“የዳታ ማዕከላት በነገ ዲጂታል መሰረተ ልማቶች ግንባታ ውስጥ ያላቸው ቁልፍ ሚና” የአውደ ርዕዩ መሪ ሀሳብ ነው።

በዓለም ላይ ግዙፍ ከሚባሉት የቴክኖሎጂ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ጀማሪ ስራ ፈጠራ ትዕይንቶች አንዱ በሆነው ጂአይቴክስ ከ180 ሀገራት የተወጣጡ ከ6 ሺህ 500 በላይ አቅራቢዎች፣ 1 ሺህ 800 ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች እና 1 ሺህ 200 ባለሀብቶች ተሳታፊ ሆነዋል።

ጂአይቴክስ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች፣ የመንግስት ተቋማት፣ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ኢኖቬተሮች እና ተመራማሪዎችን በአንድ መድረክ ያገናኘ ነው።


ዓለም አቀፍ አውደ ርዕዩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት፣ የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ኢኖቬሽን፣ የጤና እና ባዮ ቴክኖሎጂዎች፣ ኮሙኒኬሽን፣ ሮቦቲክስ፣ የቀጣዩ ትውልድ ቴክኖሎጂዎች፣ የኮምፒዩተር ስርዓቶች እና ማሽኖችን ጨምሮ በርካታ ዘርፎችን ይዟል።

በጂአይቴክስ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች እና ባለሀብቶች እየተሳተፉ እንደሚገኙ Pulse of Africa ሚዲያ ከስፍራው ዘግቧል።

እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው ዓለም አቀፍ ሁነት በዋናነት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ መሰረት ያደረጉ ፈጠራዎች እንደሚቀርቡና በዘርፉ ላይ ትኩረት ያደረጉ ውይይቶች እንደሚካሄዱም ተመላክቷል።

እንደ ተባበሩት መንግስታት የንግድ እና ልማት ጉባዔ (አንክታድ) ጥናት ከሆነ እንደ አውሮፓውያኑ የዘመን ቀመር በ2033 የሰው ሰራሽ አስተውሎት ገበያ ወደ 4 ነጥብ 8 ትሪሊዮን የአሜሪካን ዶላር ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል።

አሁን ላይ የ757 ነጥብ 58 ቢሊዮን ዶላር የገበያ ድርሻ እንዳለው ይገመታል።

አንክታድ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቴክኖሎጂ ገበያው ያለው ድርሻ ወደ 29 በመቶ ማደጉን ጠቅሶ፤ ይህም ኤአይ በዘርፉ እያደገ የመጣውን ከፍተኛ አቅም የሚያመላክት ነው።

ይህ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቀጣይ ጊዜያት በዓለም ላይ የሚኖረውን ተፅእኖ ያሳያል።

የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) እ.አ.አ 1981 አንስቶ እየተካሄደ የሚገኝ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ሁነት ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026