🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም የኢንተርኔት አገልግሎትን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የሚረዳ ዘ ኔክሰስ የተሰኘ አገልግሎት ይፋ አድርጓል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ አገልግሎቱን አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ በዚሁ ወቅት፤ በኢትዮጵያ 85 ነጥብ 9 ሚሊዮን የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች እንዳሉ አመልክተው፤ ከእነዚህ ውስጥ 47 ሚሊዮኑ ብቻ ኢንተርኔት እንደሚጠቀም አስታውቀዋል፡፡
ለዚህም የተለያዩ ምክንያቶች ቢኖሩም የመጠቀሚያ ዲቫይሶች (መሳሪያዎች) ዋጋ መወደድ ዋነኛው ምክንያት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ዘ ኔክሰስ የተሰኘ አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡
አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ የክላውድ ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ ፊውቸር ፎኖች(የእጅ ስልኮች) ላፕቶፖች፣ ታብሌቶችና ዴስክ ቶፕ ኮምፒዩተሮች በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ማቅረቡን ገልጸዋል።
መሳሪያዎቹን የሚጠቀሙ ደንበኞች የኢትዮ ቴሌኮምን ክላውድ በቀጥታ በመጠቀም የኢንተርኔት አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸው መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት፣ ትምህርትን ጨምሮ የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶች በኢንተርኔት እንደሚሰጡ ጠቁመው፤ በዚህ ረገድ ዘ ኔክስ አገልግሎት ወደ ስራ መግባት ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026