🔇Unmute
ጂንካ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-የደመወዝ ማሻሻያው የዜጎችን ችግር ለመፍታትና የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት የመንግስት ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ከተማ የመንግስት ሠራተኞች ተናገሩ።
የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻልና የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል በበጀት ዓመቱ ከመስከረም ወር ጀምሮ ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መወሰኑ ይታወሳል።
የደመወዝ ማሻሻያው በተለይም ዝቅተኛ ተከፋይ የሆኑ የመንግስት ሠራተኞችን የኑሮ ጫናን በማቃለል ረገድ ትርጉም ያለው መሆኑ ይታወቃል።
በዚሁ ጉዳይ ላይ በጂንካ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያው የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት የመንግስት ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን በማንሳት በጭማሪው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
የደመወዝ ማሻሻያው በአሁኑ ወቅት ያለውን የኑሮ ጫና ያገናዘበ በመሆኑ ኑሮን ለመቋቋም የሚያግዝ መሆኑን አንስተው ስራቸውን በተሻለ ትጋት ለማከናወን መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑንም ተናግረዋል።
በአሪ ዞን ገቢዎች መምሪያ የምጣኔ ሀብት ጥናት ባለሙያ ሀብታሙ ዲዳ፤ መንግስት የወቅቱን የኑሮ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ለመንግስት ሠራተኛው የደመወዝ ማሻሻያ ማድረጉ ተገቢና ወቅታዊ መሆኑን ገልጸዋል።

የደመወዝ ማሻሻያው የኑሮ ጫናን ከማቃለልም ባለፈ ለስራ ጥሩ ተነሳሽነትን ያመጣ ስለመሆኑም አንስተዋል።
በክልሉ ትምህርት ቢሮ ውስጥ የሚሰሩት አቶ ሳሙኤል ሻሌቦ እና በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የጂንካ ቅርንጫፍ የሚሰሩት ወንድማገኝ በቀለ፣ የደመወዝ ማሻሻያው እየጨመረ የመጣውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋምና ለሰራተኛው የስራ ብርታት ተጨማሪ አቅም መሆኑን ነው የገለጹት።

የአሪ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ አሸብር ገልሶ፤ የደመወዝ ጭማሪው የኑሮ ሁኔታን ታሳቢ ያደረገና ሰራተኞችን ይበልጥ ለማበረታታት ያለመ መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም ሠራተኞች ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት በማገልገል እንዲሁም ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወን ለተደረገው ጭማሪ ተግባራዊ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026