🔇Unmute
ጂንካ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-የደመወዝ ማሻሻያው የዜጎችን ችግር ለመፍታትና የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት የመንግስት ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ከተማ የመንግስት ሠራተኞች ተናገሩ።
የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻልና የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል በበጀት ዓመቱ ከመስከረም ወር ጀምሮ ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መወሰኑ ይታወሳል።
የደመወዝ ማሻሻያው በተለይም ዝቅተኛ ተከፋይ የሆኑ የመንግስት ሠራተኞችን የኑሮ ጫናን በማቃለል ረገድ ትርጉም ያለው መሆኑ ይታወቃል።
በዚሁ ጉዳይ ላይ በጂንካ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያው የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት የመንግስት ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን በማንሳት በጭማሪው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
የደመወዝ ማሻሻያው በአሁኑ ወቅት ያለውን የኑሮ ጫና ያገናዘበ በመሆኑ ኑሮን ለመቋቋም የሚያግዝ መሆኑን አንስተው ስራቸውን በተሻለ ትጋት ለማከናወን መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑንም ተናግረዋል።
በአሪ ዞን ገቢዎች መምሪያ የምጣኔ ሀብት ጥናት ባለሙያ ሀብታሙ ዲዳ፤ መንግስት የወቅቱን የኑሮ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ለመንግስት ሠራተኛው የደመወዝ ማሻሻያ ማድረጉ ተገቢና ወቅታዊ መሆኑን ገልጸዋል።

የደመወዝ ማሻሻያው የኑሮ ጫናን ከማቃለልም ባለፈ ለስራ ጥሩ ተነሳሽነትን ያመጣ ስለመሆኑም አንስተዋል።
በክልሉ ትምህርት ቢሮ ውስጥ የሚሰሩት አቶ ሳሙኤል ሻሌቦ እና በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የጂንካ ቅርንጫፍ የሚሰሩት ወንድማገኝ በቀለ፣ የደመወዝ ማሻሻያው እየጨመረ የመጣውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋምና ለሰራተኛው የስራ ብርታት ተጨማሪ አቅም መሆኑን ነው የገለጹት።

የአሪ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ አሸብር ገልሶ፤ የደመወዝ ጭማሪው የኑሮ ሁኔታን ታሳቢ ያደረገና ሰራተኞችን ይበልጥ ለማበረታታት ያለመ መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም ሠራተኞች ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት በማገልገል እንዲሁም ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወን ለተደረገው ጭማሪ ተግባራዊ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026