🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-ካናዳ ከኢትዮጵያ ጋር በተለያዩ ዘርፎች ያላትን ኢኮኖሚያዊ ትብብር በማስፋት አጠናክራ እንደምትቀጥል በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙት የካናዳ አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ ገለጹ።
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተ መንግስት የተለያዩ ሀገራትን አዳዲስ አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀብለዋል።
የሹመት ደብዳቤ ካቀረቡት አምባሳደሮች መካከል የካናዳው አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ ይገኙበታል።

አምባሳደር ሲማርድ በዚሁ ወቅት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ እና ካናዳ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት አላቸው።
የሁለቱ አገሮች ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤ ካናዳ ለኢትዮጵያ ከዋና ዋናዎቹ የልማት አጋሮች አንዷ መሆኗን ገልጸዋል።
አምባሳደር ሲማርድ እንደገለጹት፤ ካናዳ ከኢትዮጵያ ጋር በኤሮስፔስ፣ ማዕድን፣ ትምህርት እና በሌሎችም መስኮች ትብብሯን አጠናክራ ትቀጥላለች።
በተጨማሪም ኢትዮጵያና ካናዳ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላም እና መረጋጋትን ለማረጋገጥ ተቀራርበው እየሠሩ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይህንንም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
በቀጣይ ሁለቱ አገራት አጋርነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አምባሳደሩ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026