የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ካናዳ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ ትብብር አጠናክራ ትቀጥላለች- አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ 

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-ካናዳ ከኢትዮጵያ ጋር በተለያዩ ዘርፎች ያላትን ኢኮኖሚያዊ ትብብር በማስፋት አጠናክራ እንደምትቀጥል በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙት የካናዳ አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ ገለጹ።

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተ መንግስት የተለያዩ ሀገራትን አዳዲስ አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀብለዋል።

የሹመት ደብዳቤ ካቀረቡት አምባሳደሮች መካከል የካናዳው አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ ይገኙበታል።


አምባሳደር ሲማርድ በዚሁ ወቅት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ እና ካናዳ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት አላቸው።

የሁለቱ አገሮች ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤ ካናዳ ለኢትዮጵያ ከዋና ዋናዎቹ የልማት አጋሮች አንዷ መሆኗን ገልጸዋል።

አምባሳደር ሲማርድ እንደገለጹት፤ ካናዳ ከኢትዮጵያ ጋር በኤሮስፔስ፣ ማዕድን፣ ትምህርት እና በሌሎችም መስኮች ትብብሯን አጠናክራ ትቀጥላለች።

በተጨማሪም ኢትዮጵያና ካናዳ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላም እና መረጋጋትን ለማረጋገጥ ተቀራርበው እየሠሩ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይህንንም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

በቀጣይ ሁለቱ አገራት አጋርነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አምባሳደሩ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026