🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፡- በወላይታ ዞን የሕዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በግብር አሰባሰብ ላይ እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት መሻሻል እያሳዩ መሆኑ ተገለጸ።
የዞኑ ገቢዎች መምሪያ የ2018 ሩብ የበጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ፣ የገጠር መሬት መጠቀሚያ ኪራይ እና የእርሻ ስራ ገቢ ግብር አሰባሰብ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የዞኑ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ታደሰ ፤ በበጀት ዓመቱ ከመደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል።
በዚህም በመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።
የገቢ አቅም ልየታና የአሰባሰብ ሂደቱ በቴክኖሎጂ ታግዞ ቀልጣፋ የማድረጉ ተግባር መሻሻል ማምጣቱን ተናግረዋል።
በቀጣይም የገጠር መሬት መጠቀሚያ ኪራይና የእርሻ ስራ ገቢ ግብር አሰባሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አብራርተዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ(ረዳት ፕሮፌሰር)፤ የዞኑን ሕዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በግብር አሰባሰብ ላይ እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት መሻሻል እያሳዩ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በዞኑ ኢኮኖሚው ከሚያመነጨ አቅም መነሻ ያደረገ ገቢ በመሰብሰብ ወጪን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረጉ ጥረቶች ውጤት እያመጡ መሆኑን ጠቅሰው፤ ካለው የገቢ አማራጭ አንጻር ብዙ ሊሰራ ይገባል ብለዋል ።
በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ለማዘመን እየተደረገ ያለው ጥረት መጠናከር እንዳለበትም አሳስበዋል።
በመድረኩ ላይ የዞን፣የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር ስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026