🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፡- በወላይታ ዞን የሕዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በግብር አሰባሰብ ላይ እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት መሻሻል እያሳዩ መሆኑ ተገለጸ።
የዞኑ ገቢዎች መምሪያ የ2018 ሩብ የበጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ፣ የገጠር መሬት መጠቀሚያ ኪራይ እና የእርሻ ስራ ገቢ ግብር አሰባሰብ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የዞኑ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ታደሰ ፤ በበጀት ዓመቱ ከመደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል።
በዚህም በመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።
የገቢ አቅም ልየታና የአሰባሰብ ሂደቱ በቴክኖሎጂ ታግዞ ቀልጣፋ የማድረጉ ተግባር መሻሻል ማምጣቱን ተናግረዋል።
በቀጣይም የገጠር መሬት መጠቀሚያ ኪራይና የእርሻ ስራ ገቢ ግብር አሰባሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አብራርተዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ(ረዳት ፕሮፌሰር)፤ የዞኑን ሕዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በግብር አሰባሰብ ላይ እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት መሻሻል እያሳዩ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በዞኑ ኢኮኖሚው ከሚያመነጨ አቅም መነሻ ያደረገ ገቢ በመሰብሰብ ወጪን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረጉ ጥረቶች ውጤት እያመጡ መሆኑን ጠቅሰው፤ ካለው የገቢ አማራጭ አንጻር ብዙ ሊሰራ ይገባል ብለዋል ።
በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ለማዘመን እየተደረገ ያለው ጥረት መጠናከር እንዳለበትም አሳስበዋል።
በመድረኩ ላይ የዞን፣የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር ስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026