🔇Unmute
አሶሳ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ሶሰት ወራት ውጤታማ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን አስታወቁ።
የክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እየተገመገመ ነው።

በግምገማ መድረኩ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን እንደተናገሩት፤ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የትምህርት ንቅናቄ በስፋት የተከናወነበት፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትና የግብርና ስራ የተጠናከረበት ነው።
የሕብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአጭር ጊዜ ወደ ስራ እንዲገባ መደረጉንና በዲጂታል የታገዘ አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል።
በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የማዕድን ዘርፉን ለማልማት እየተከናወነ ባለው ቅንጅታዊ ስራ 1ሺህ 709 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን ጠቅሰዋል።
በመጀመሪያ ሩብ የበጀት ዓመት ለተከናወኑ ስራዎች ውጤታማነት ቅንጅታዊ አሰራር በመተግበሩ እንደሆነ ተናግረዋል።
የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ቃሲም ኢብራሂም እየቀረበ ሲሆን፤ በሪፖርቱ ላይ ጥልቅ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026