የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት ውጤታማ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ተከናውነዋል - ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ሶሰት ወራት ውጤታማ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን አስታወቁ።

የክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እየተገመገመ ነው።


በግምገማ መድረኩ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን እንደተናገሩት፤ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የትምህርት ንቅናቄ በስፋት የተከናወነበት፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትና የግብርና ስራ የተጠናከረበት ነው።

የሕብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአጭር ጊዜ ወደ ስራ እንዲገባ መደረጉንና በዲጂታል የታገዘ አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል።

በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የማዕድን ዘርፉን ለማልማት እየተከናወነ ባለው ቅንጅታዊ ስራ 1ሺህ 709 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን ጠቅሰዋል።

በመጀመሪያ ሩብ የበጀት ዓመት ለተከናወኑ ስራዎች ውጤታማነት ቅንጅታዊ አሰራር በመተግበሩ እንደሆነ ተናግረዋል።

የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ቃሲም ኢብራሂም እየቀረበ ሲሆን፤ በሪፖርቱ ላይ ጥልቅ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026