🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ የኦፕሬሽን ጉዳዮች ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሚስ አና ብጄርዴ ጋር በቅድመ-ልማት ፕሮጀክቶች፣ በመካሄድ ላይ ያሉ የሪፎርም ስራዎች እና አዳዲስ የፋይናንሺንግ ዘዴዎች ላይ ያለውን ትብብር ለማጠናከር ከፍተኛ ደረጃ ያለው ውይይት አደርገዋል።
ውይይቱ እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2025 ከተካሄደው የአለም ገንዘብ ድርጅትና የዓለም ባንክ ግሩፕ አመታዊ ስበሰባ ጎን ለጎን ነው።
በዚህ ወቅት አቶ አህመድ ሽዴ የዓለም ባንክ የኢትዮጵያን የልማት አጀንዳ ለማሳደግ ያለውን ከፍተኛ ሚና እውቅና በመስጠት እየተደረገ ለሚገኘው የቴክኒክ እና የፋይናንስ ድጋፍ አመስግነዋል።
ባንኩ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በማዘመን፣ ምርታማነትን በማሳደግ፣ አዳዲስ የእድገት መንገዶችን በመፍጠርና የግሉ ዘርፍ ተሳትፎን በማጎልበት የስራ እድል ለመፍጠር እና የኑሮ ደረጃን ለማሻሻል ያለውን አስተዋፅዖም አንስተዋል።
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ አጋርነት እና ከፍተኛ ድጋፍ እየተካሄዱ በሚገኙ ዋና ዋና ዘርፎች ከ15 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት ድጋፍን በማረጋገጥ ላሳየው አጋርነት ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የስራ እድል ፈጠራን፣ ዘላቂ መሠረተ ልማቶችንና የሰው ሃይል ልማትን ለማስቀጠል የባንኩ ቀጣይ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው መግለጻቸውም ተመላክቷል።
የአለም ባንክ የስትራቴጂክ አጋርነት ኦፕሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሚስ አና ብጄርዴ በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግስት ባካሄደው የሪፎርም አጀንዳ ምክንያት የተገኘውን ውጤት አድንቀዋል።
በሪፎርሙ አማካኝነት የዋጋ ንረት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን፣ ከፍተኛ የወጪ ንግድ መጨመሩን በተለይም በወርቅ፣ የተሻለ የሀገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብ፣ የፊስካል ማገገምን የሚያጠናክር እንዲሁም ከጊዜ ወደ ጊዜ ምቹ የንግድ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ለማሳያነት አንስተዋል።
ዋና ዋና የሪፎርም ርምጃዎችን በመተግበር ረገድ መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚያበረታቱም ገልጸዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026