🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ የኦፕሬሽን ጉዳዮች ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሚስ አና ብጄርዴ ጋር በቅድመ-ልማት ፕሮጀክቶች፣ በመካሄድ ላይ ያሉ የሪፎርም ስራዎች እና አዳዲስ የፋይናንሺንግ ዘዴዎች ላይ ያለውን ትብብር ለማጠናከር ከፍተኛ ደረጃ ያለው ውይይት አደርገዋል።
ውይይቱ እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2025 ከተካሄደው የአለም ገንዘብ ድርጅትና የዓለም ባንክ ግሩፕ አመታዊ ስበሰባ ጎን ለጎን ነው።
በዚህ ወቅት አቶ አህመድ ሽዴ የዓለም ባንክ የኢትዮጵያን የልማት አጀንዳ ለማሳደግ ያለውን ከፍተኛ ሚና እውቅና በመስጠት እየተደረገ ለሚገኘው የቴክኒክ እና የፋይናንስ ድጋፍ አመስግነዋል።
ባንኩ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በማዘመን፣ ምርታማነትን በማሳደግ፣ አዳዲስ የእድገት መንገዶችን በመፍጠርና የግሉ ዘርፍ ተሳትፎን በማጎልበት የስራ እድል ለመፍጠር እና የኑሮ ደረጃን ለማሻሻል ያለውን አስተዋፅዖም አንስተዋል።
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ አጋርነት እና ከፍተኛ ድጋፍ እየተካሄዱ በሚገኙ ዋና ዋና ዘርፎች ከ15 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት ድጋፍን በማረጋገጥ ላሳየው አጋርነት ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የስራ እድል ፈጠራን፣ ዘላቂ መሠረተ ልማቶችንና የሰው ሃይል ልማትን ለማስቀጠል የባንኩ ቀጣይ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው መግለጻቸውም ተመላክቷል።
የአለም ባንክ የስትራቴጂክ አጋርነት ኦፕሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሚስ አና ብጄርዴ በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግስት ባካሄደው የሪፎርም አጀንዳ ምክንያት የተገኘውን ውጤት አድንቀዋል።
በሪፎርሙ አማካኝነት የዋጋ ንረት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን፣ ከፍተኛ የወጪ ንግድ መጨመሩን በተለይም በወርቅ፣ የተሻለ የሀገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብ፣ የፊስካል ማገገምን የሚያጠናክር እንዲሁም ከጊዜ ወደ ጊዜ ምቹ የንግድ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ለማሳያነት አንስተዋል።
ዋና ዋና የሪፎርም ርምጃዎችን በመተግበር ረገድ መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚያበረታቱም ገልጸዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026