የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣንን ለመቋቋም ስምምነት ላይ ተደረሰ

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 13/2018(ኢዜአ)፦የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን የቴክኒክ ኮሚቴ እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት መድረክ የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣንን ለማቋቋም በመስማማት ተጠናቋል።

የቴክኒክ ኮሚቴው እና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱ መድረክ ጅቡቲን፣ ኢትዮጵያን፣ ደቡብ ሱዳንን እና ዩጋንዳን ያቀፈ ነው።


የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣንን ለመመስረት በጅቡቲ ከኦክቶበር 21-22/25 ለሁለት ቀናት ውይይት ሲያደርግ የቆየው የቴክኒክ ኮሚቴ እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኮርደር አስተዳደር ባለስልጣን መቋቋም ላይ ተስማምቷል።

ከሁለት ሳምንት በኋላ በኢትዮጵያ በመገናኘት የአስተዳደሩን ሟቋቋሚያ ስምምነት ለመፈራረም በመግባባት እና የስምምነት ቃለ-ጉባኤ በመፈራረም ተጠናቋል።

የ”DESSU” ኮሪደር በአራቱ ሀገራት መካከል የውጪ ንግድ መንገዶችን በቀላሉ ለማገናኘት፣ መንገድ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን ለማሳለጥ ያለመ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.