🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 13/2018(ኢዜአ)፦የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን የቴክኒክ ኮሚቴ እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት መድረክ የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣንን ለማቋቋም በመስማማት ተጠናቋል።
የቴክኒክ ኮሚቴው እና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱ መድረክ ጅቡቲን፣ ኢትዮጵያን፣ ደቡብ ሱዳንን እና ዩጋንዳን ያቀፈ ነው።

የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣንን ለመመስረት በጅቡቲ ከኦክቶበር 21-22/25 ለሁለት ቀናት ውይይት ሲያደርግ የቆየው የቴክኒክ ኮሚቴ እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኮርደር አስተዳደር ባለስልጣን መቋቋም ላይ ተስማምቷል።
ከሁለት ሳምንት በኋላ በኢትዮጵያ በመገናኘት የአስተዳደሩን ሟቋቋሚያ ስምምነት ለመፈራረም በመግባባት እና የስምምነት ቃለ-ጉባኤ በመፈራረም ተጠናቋል።
የ”DESSU” ኮሪደር በአራቱ ሀገራት መካከል የውጪ ንግድ መንገዶችን በቀላሉ ለማገናኘት፣ መንገድ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን ለማሳለጥ ያለመ ነው።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026