🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 17/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የበጀት ዓመት 21 ከተሞች ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ እንዲገቡ የሚያስችሉ አሠራሮች መጠናከራቸውን ከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በሚኒስቴሩ የአከታተም ጥናትና የሕግ ማዕቀፍ ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ አስማማው ምኑዬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ አዳማ፣ ባሕርዳርና ሐዋሳ ከተሞች ቀደም ብለው ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ ገብተዋል።
በያዝነው የበጀት ዓመትም 21 ከተሞች ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ እንዲገቡ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የስማርት ሲቲ ግንባታና መመዘኛ ሠነድ ተዘጋጅቶ ለክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች መሰራጨቱን ጠቅሰዋል።
ስማርት ኢኮኖሚ፣ ስማርት አሥተዳደር፣ ስማርት አካባቢ፣ ስማርት ሞቢሊቲ፣ ስማርት ነዋሪና ስማርት አኗኗር የተሰኙ ስድስት የስማርት ሲቲ ምሰሦዎች በስማርት ሲቲ ስትራቴጂው ላይ መቀመጣቸውንም አስረድተዋል።
በእያንዳንዱ ምሰሦ ላይም ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አሠራሮች መኖራቸውን ነው ያስረዱት።
ስማርት ሲቲ ነዋሪዎች ባሉበት ሆነው በ ‘ኦንላይን’ እንዲሁም እንደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባሉ አሠራሮች በርካታ ተቋማትን በአንድ ስፍራ ማግኘት የሚያስችል መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከተሞች ጽዱ፣ የእግረኛና ብስክሌት መንገዶች፣ የማረፊያ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ እንዲኖራቸው እንደሚያስችልም ገልጸዋል።
ስማርቲ ሲቲ ተጀምሮ የሚያልቅ ሳይሆን ቴክኖሎጂው ባደገ ቁጥር የሚያድግ ሂደት መሆኑን ገልጸው፤ የአንድ ተቋም ሥራ ስላልሆነ ተቋማት፣ ባለድርሻ አካላትና ሕብረተሰቡ ትብብሩን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026