የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ስማርት ሲቲን የማስፋት ሥራ

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 17/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የበጀት ዓመት 21 ከተሞች ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ እንዲገቡ የሚያስችሉ አሠራሮች መጠናከራቸውን ከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በሚኒስቴሩ የአከታተም ጥናትና የሕግ ማዕቀፍ ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ አስማማው ምኑዬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ አዳማ፣ ባሕርዳርና ሐዋሳ ከተሞች ቀደም ብለው ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ ገብተዋል።

በያዝነው የበጀት ዓመትም 21 ከተሞች ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ እንዲገቡ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የስማርት ሲቲ ግንባታና መመዘኛ ሠነድ ተዘጋጅቶ ለክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች መሰራጨቱን ጠቅሰዋል።

ስማርት ኢኮኖሚ፣ ስማርት አሥተዳደር፣ ስማርት አካባቢ፣ ስማርት ሞቢሊቲ፣ ስማርት ነዋሪና ስማርት አኗኗር የተሰኙ ስድስት የስማርት ሲቲ ምሰሦዎች በስማርት ሲቲ ስትራቴጂው ላይ መቀመጣቸውንም አስረድተዋል።

በእያንዳንዱ ምሰሦ ላይም ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አሠራሮች መኖራቸውን ነው ያስረዱት።

ስማርት ሲቲ ነዋሪዎች ባሉበት ሆነው በ ‘ኦንላይን’ እንዲሁም እንደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባሉ አሠራሮች በርካታ ተቋማትን በአንድ ስፍራ ማግኘት የሚያስችል መሆኑን አስገንዝበዋል።

ከተሞች ጽዱ፣ የእግረኛና ብስክሌት መንገዶች፣ የማረፊያ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ እንዲኖራቸው እንደሚያስችልም ገልጸዋል።

ስማርቲ ሲቲ ተጀምሮ የሚያልቅ ሳይሆን ቴክኖሎጂው ባደገ ቁጥር የሚያድግ ሂደት መሆኑን ገልጸው፤ የአንድ ተቋም ሥራ ስላልሆነ ተቋማት፣ ባለድርሻ አካላትና ሕብረተሰቡ ትብብሩን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.