የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ያሳድጋል 

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ፋይዳው የጎላ መሆኑን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ።

በቅርቡ ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት ከሀይል አማራጭነት የዘለለ የተለያዩ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ።

ከእነዚህ ጠቀሜታዎች መካከል አንዱ የኒኩሌር ህክምና አገልግሎት ይገኝበታል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መምህር፣ ሀኪም፣ ተመራማሪና የካንሰር ሕክምና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን ሁነኛው ለኢዜአ እንደገለፁት የኒኩሌር ፕላንቱ በሕክምናው ዘርፍ ለኢትዮጵያ ትልቅ እድል ይዞ የሚመጣ ነው።

በተለይ በዋናነት የካንሰር በሽታን ለማከም ያለው ፋይዳ ላቅ ያለ በመሆኑ የህክምና አገልግሎቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደርሰዋል ብለዋል።

አክለውም ለራዲዮ ቴራፒ ሕክምና የሚውሉ መድሀኒቶችን ለማምረትና የቆይታ ጊዜያቸው ከስምንት ቀን የማይበልጡ መድሀኒቶችን ብልሽት መፍታት ያስችላል ነው ያሉት።

ከኒኩሌር ጋር በተያያዘ መንግስት የወሰደው ኢንሼቲቭ ከህክምና አገልግሎቱ ባለፈ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለው ፋይዳም ከፍተኛ በመሆኑ መበረታታት እንዳለበት ዶክተር ሰለሞን ተናግረዋል።


ሌላው የዩኒቨርሲቲው መምህርና የህጻናት ካንሰር ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሙሉአለም ንጉሴ በበኩላቸው ያደጉ ሀገሮች የኒኩሌር ሕክምናን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠቀሙበት አንስተዋል።

የኒኩሌር ሀይል ለአዋቂም ሆነ ለሕጻናት ሕክምና የበሽታውን ሁኔታና ያለበትን ደረጃ ለይቶ ለማከም ያለው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ለሕክምናው ዘርፍ ጭምር ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ብለዋል።

የኒኩሌር ሀይል ለካንሰር ሕክምና አገልግሎት ሦስት ዋና ዋና ፋይዳ አለው ያሉት ባለሙያው የካንሰር አይነቱንና የስርጭቱን መጠን እንዲያውቅ ይረዳዋል ነው ያሉት።

ሕመምተኛውም የበሽታው አይነትና ስርጭትን መሰረት ያደረገ ሕክምና እንዲያገኝ እንደሚያስችለው ገልጸዋል።

ለካንሰር ሕሙማን የኒኩሌር ሕክምና በሀገር ውስጥ ስለማይሰጥ ሕክምናውን ለማግኘት ወደ ውጪ እንደሚላኩ የገለጹት ዶክተር ሙሉአለም በዚህም ምክንያት ለወጪና እንግልት ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።


የኒኩሌር ሕክምና ከሌሎቹ የሲቲ ስካን፣ ኤም አር አይ እና ሌሎች መሳሪያዎች አንጻር ያለውን በሽታ ለይቶ ማሳየት ብቻ ሳይሆን ያደረሰውን የጉዳት መጠን ጭምር ለይቶ የሚያሳይ ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ክብሩ ክፍሌ ናቸው።

በካንሰር የተጠቃ የሰውነት አካል ምን ያህል እንደተጎዳ፣ የትኛው ክፍሉ ሥራውን በአግባቡ እያከናወነ እንደሚገኝ የሚለውን በትክክል መለየት የሚያስችል የዘመናዊ ሕክምና ትልቅ መሳሪያ መሆኑን አስረድተዋል።

እንደ ሀገር ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሸጋግር በመሆኑ መንግስት የወሰደው ተነሳሽነት ሊበረታታና ሊደገፍ ይገባል ሲሉም ምሁራኑ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026