የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው ሚና ከዓመት ዓመት እየጨመረ ነው - ሚኒስትር መላኩ አለበል

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው ሚና ከዓመት ዓመት እየጨመረ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለፁ።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪ ዕድገቱ በየዓመቱ እንዲጨምር ማድረጉንም ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅማቸው እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል።

ንቅናቄው በኢትዮጵያ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም ለማሳደግና ኢኮኖሚውን ለማጠናከር የተጀመረ ሀገራዊ ንቅናቄ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ ሀብትና የሰው ኃይል በመጠቀም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ፣ ወደ ውጭ የሚላከውን ምርት መጠን መጨመር ላይ የግንዛቤ ለውጥ ማምጣቱን አስታውቀዋል።

በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚያጋጥሙ የአጭርና የረጅም ጊዜ ችግሮችን በመፍታት የማምረት አቅምን በማጎልበትና ተኪ ምርቶችን የማምረት አቅም ማሳደጉንም ገልፀዋል።

በንቅናቄው የተከናወኑ ሥራዎች አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በማሳደግ በኩል አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ በ2014 ዓ.ም ላይ የአምራች ኢንዱስትሪው አመታዊ ዕድገት 4 ነጥብ 8 በመቶ እንደነበር አስታውሰው፤ ይህ አሃዝ በ2017 በጀት ዓመት ላይ በከፍተኛ ደረጃ በማደግ 10 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመት የአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ከ12 በመቶ በላይ ያስመዘግባል ተብሎ መተንበዩንም ተናግረዋል።

ንቅናቄው በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያስመዘገበው ያለው መሻሻል የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማጠናከር የሚያደርገውን አስተዋፅኦ በተግባር እያሳየ ይገኛል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.