🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው ሚና ከዓመት ዓመት እየጨመረ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለፁ።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪ ዕድገቱ በየዓመቱ እንዲጨምር ማድረጉንም ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅማቸው እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል።
ንቅናቄው በኢትዮጵያ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም ለማሳደግና ኢኮኖሚውን ለማጠናከር የተጀመረ ሀገራዊ ንቅናቄ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ ሀብትና የሰው ኃይል በመጠቀም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ፣ ወደ ውጭ የሚላከውን ምርት መጠን መጨመር ላይ የግንዛቤ ለውጥ ማምጣቱን አስታውቀዋል።
በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚያጋጥሙ የአጭርና የረጅም ጊዜ ችግሮችን በመፍታት የማምረት አቅምን በማጎልበትና ተኪ ምርቶችን የማምረት አቅም ማሳደጉንም ገልፀዋል።
በንቅናቄው የተከናወኑ ሥራዎች አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በማሳደግ በኩል አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ በ2014 ዓ.ም ላይ የአምራች ኢንዱስትሪው አመታዊ ዕድገት 4 ነጥብ 8 በመቶ እንደነበር አስታውሰው፤ ይህ አሃዝ በ2017 በጀት ዓመት ላይ በከፍተኛ ደረጃ በማደግ 10 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል።
በ2018 በጀት ዓመት የአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ከ12 በመቶ በላይ ያስመዘግባል ተብሎ መተንበዩንም ተናግረዋል።
ንቅናቄው በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያስመዘገበው ያለው መሻሻል የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማጠናከር የሚያደርገውን አስተዋፅኦ በተግባር እያሳየ ይገኛል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026