የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ክፍያ አማራጭ ለደንበኞቹ ምቹ አገልግሎት እየሰጠ ነው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 2ዐ/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች ክፍያ አማራጭ ለደንበኞቹ ምቹ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሆሊደይ፣ዲጅታል ሽያጭ እና ዓለም አቀፍ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ምክትል ፕሬዝዳንት ኃይለመለኮት ማሞ ገለጹ።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኦንላይን የክፍያ አማራጭ ስርዓት አቅራቢ ከሆነው ቻፓ ካምባኒ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።

የመግባቢያ ሰነዱን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሆሊደይ፣ ዲጅታል ሸያጭ እና ዓለም አቀፍ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ምክትል ፕሬዝዳንት ኃይለመለኮት ማሞ እና የቻፓ ካምፓኒ መስራችና ስራ አስኪያጅ ናኤል ሃይለማሪያም ፈርመዋል።

አቶ ኃይለመለኮት ማሞ በዚሁ ወቅት፤ አየር መንገዱ የደንበኞችን አገልግሎት ለማዘመን በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡

በዚህም በተለይ የአሰራር ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በርካታ ለውጦችን አስመዝግበዋል ነው ያሉት፡፡

በዛሬው እለት ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ ከሆነው ቻፓ ካምፓኒ ጋር የተደረገው ስምምነት የሀገር ውስጥና የውጭ ደንበኞችን የኦንላይን የክፍያ ስርዓት ይበልጥ ምቹ እና ቀልጣፋ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

ደንበኞች ሞባይል ባንኪንግን፣ቴሌ ብርንና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የበረራ ትኬቶቻቸውን በኦንላይን እንዲቆርጡ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች ደህንነቱ የተጠበቀ ክፍያን ለመፈጸም ሁነኛ አማራጭ በመሆናቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እነዚህን ቴክኖሎጂዎች መጠቀሙን አጠናክሮ ይቀጥል፤ድጋፍም ያደርጋል ነው ያሉት።

የቻፓ ካምፓኒ መስራችና ስራ አስኪያጅ ናኤል ሃይለማሪያም በበኩላቸው፤ ቴክኖሎጂው በኢትዮጵያ ውስጥ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ለአጠቃቀም ምቹ የሆነ የኦንላይን ክፍያ የሚሰጥ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ነው ብለዋል፡፡

ቴክኖሎጂው በኢትዮጵያ ውስጥ የኢ-ኮሜርስ ንግድ እንዲስፋፋ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡

ዓለም አቀፍ እና ከሀገር ውስጥ ደንበኞች ኦንላይን ክፍያዎችን መፈጸም እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026