የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ ገቢራዊ ያደረገቻቸው ፕሮጀክቶች ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ ነው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ገቢራዊ ያደረገቻቸው ፕሮጀክቶች ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ ነው ሲሉ አፍሪካዊያን ምሁራን ገለጹ።

ፕሮጀክቶቹ አፍሪካን እና ቀጣናውን በኢኮኖሚ ለማስተሳሰር ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸውም ምሁራኑ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በዜጎች ርብርብ በራስ አቅም ገንብታ አጠናቃለች።

የኒውክሌር ኃይልን ለሠላማዊ ግልጋሎት ለማዋል የሚያስችል ፕሮጀክት፣የነዳጅ ማጣሪያ እና የተፈጥሮ ጋዝና ግዙፍ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ለማካሄድ ተግባራዊ እርምጃዎችንም ወስዳለች።

በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ-ቻይና ጥናት ማዕከል ዳይሬክተር ዴቪድ ሞኛዬ(ፕ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ኢትዮጵያ በኢኮኖሚው መስክ እየተገበረቻቸው ያሉ የልማት ኢኒሼቲቮች ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ ናቸው።


ከመሰረተ ልማት አቅርቦት አኳያም በአዲስ አበባ የታየው ለውጥ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም የውጤታማ አመራር መኖር ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በራስ አቅም ገንባታ እውን ማድረጓ ትልቅ እርምጃ መሆኑን የገለጹት ፕሮፌሰሩ ቀጣናውን በኃይል ለማስተሳሰር ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከድህነት ለመላቀቅ በምግብ ዋስትና በኃይል አቅርቦት ላይ ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ከኢትዮጵያ አልፎ በቀጣናው ሀገራት በጎ ተጽዕኖ ያላቸው መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ የልማት ኢኒሼቲቭ ከአፍሪካ አጀንዳ 2063 ጋር የተሳሰረ መሆኑን ገልጸው፤ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ሞዴል ሆኖ የሚያገለግል ነው ብለዋል።


በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የፖሊሲ ተንታኝ ፓ ኪዌሲ ሄቶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ከኃይል አቅርቦት ባለፈ ማዳበሪያን በሀገር ውስጥ ለማምረት እንቅስቃሴ መጀመሯ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የልማት ኢኒሼቲቮች ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ኢኮኖሚ መለወጥ አዎንታዊ ሚና እንዳላቸውም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026