የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምርምር የወጡ የስንዴ ዝርያዎችን በማስተዋወቅ ለስንዴ ምርታማነት ትኩረት ተሰጥቷል - ሚኒስቴሩ

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ጥቅምት 22/2018(ኢዜአ)፦ በምርምር የወጡ የስንዴ ዝርያዎችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በማስተዋወቅ ለስንዴ ምርትና ምርታማነት ትኩረት መሰጠቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የስንዴ እሴት ሰንሰለት ልማት ፕሮጀክት አማካኝነት ለግብርና ባለሙያዎች የተዘጋጀ ስልጠና ዛሬ በሰማራ ከተማ ተሰጥቷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በግብርና ሚኒስቴር የፕሮጀክቱ ብሔራዊ አስተባባሪ አብዱሰመድ አብዱ እንዳሉት፣ ፕሮጀክቱ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ጉልህ ሚና አለው።

ስንዴ ለአብዛኛው የማህበረሰብ ክፍል የምግብ ሉአላዊነቱን የሚያረጋግጥ ሰብል በመሆኑ ከስንዴ ልማት አርሶ አደሩ የተሻለ ተጠቃሚ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ፕሮጀክቱ በኦሮሚያ፣ አማራ፣ ሶማሌና አፋር ክልሎች ባሉ 76 ወረዳዎች ላይ እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው፤ በአፋር ክልል አፋምቦ፣ አሚበራና ዱብቲ ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

እስካሁንም በዱብቲ ወረዳ በሰፋፊ መሬቶች ላይ ውስን ጉልበት በመጠቀም የሜካናይዜሽን እርሻ ለማከናወን የቦታ ልየታ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል።

በፕሮጀክቱ በአፋር ክልል በተመረጡ አካባቢዎች በምርምር የወጡ የስንዴ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ የማድረስ ሥራ እንደሚከናውን ገልፀው፣ ከስንዴ በተጨማሪ ለአኩሪ አተርና ለሩዝ ዝርያዎች ትኩረት መሰጠቱንም አመልክተዋል።

በአፋር ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ የሰብል ልማት ዳይሬክተር ሃመዱ መሐመድ በክልሉ በአዋሽ ወንዝ ተፋሰሰ ላይ በሚገኙ 11 ወረዳዎች የስንዴ ልማት ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የመስኖ ውሃን በመጠቀም በክልሉ የስንዴ ልማት በባለሃብቶች፣ በከፊል አርብቶ አደሮችና በማህበራት አማካኝነት እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል።

የስንዴ ምርታማነትን ለማሳደግ የአፋር ምርጥ ዘር ኢንተርኘራይዝ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት እንዳሉ ጠቅሰው፣ ፕሮጀክቱ በስንዴ ልማት ላይ ምርታማነትን ለማሳደግ የላቀ ሚና እንደሚኖረው ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026