የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በሀገር ደረጃ የተወጠኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ዕድገት የሚያፋጥኑ ናቸው

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 23/2018 (ኢዜአ):-በሀገር ደረጃ የተወጠኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማፋጠን ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪ ዘሪሁን ተምሳስ (ዶ/ር) ተናገሩ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉባ ላይ ይፋ የተደረጉት ፕሮጀክቶች የሀገሪቷን የኢኮኖሚ መሠረቶች ወደ ብዝሃ ዘርፍ በማምጣት የተጀመረውን ሀገራዊ የብልፅግና ጉዞ በአስተማማኝ መንገድ ለማስቀጠል እንደሚያስችሉ ተመልክቷል።

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪ ዘሪሁን ተምሳስ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ መንግስት የወጠናቸው የልማት ስራዎች የሀገርን ከፍታ የሚያረጋግጡ ናቸው።

ወደ 30 ቢሊዮን ዶላር በጀት የሚፈጁት እነዚሁ ግዙፍ ፕሮጀክቶች በየትኛውም የሀገራችን ዘመን ያልተሞከሩና የሀገርን የለውጥና የዕድገት ጉዞ በአስተማማኝ መሠረት ላይ ለማዋቀር የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ምሁሩ እንዳወሱት፤ በቢሾፍቱ የሚገነባው ግዙፉ የአውሮፕላን ማረፊያ፣የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የኒውክለር ማበልፀጊያ ፕላንት፣ የነዳጅ ማጣሪያና የጋዝ ፋብሪካን ጨምሮ ሌሎችም ፕሮጀክቶች የሀገርን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ይበልጥ በማሳለጥ የዜጎችን ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ የሚያሳድጉ ናቸው።

በተጨማሪም የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት እና በማስገኘት የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለዋጋ ንረት መፍትሄ እንደሚያመጡ ነው ያመለከቱት።

ፕሮጀክቶቹ ኢትዮጵያ ወደ ብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ መዋቅር ለመሸጋገር የጀመረችውን ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ መሰረት እንደሚጥሉም ተናግረዋል።

ይህም ኢኮኖሚን በማሳደግ የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥ አክለዋል ።

እንደ ምሁሩ ማብራሪያ፤መንግስት በሀገሪቱ ታሪክ ግዙፍና አሻጋሪ ፕሮጀክቶች መጀመሩ የአሁንና የቀጣዩ ትውልድ ታላቅ ብስራትና ኩራት ነው።

በመሆኑም እነዚህ አሻጋሪ ፕሮጀክቶች የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስገኙ ዜጎች እና ምሁራን ልክ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁሉ ርብርባቸውን እንዲያጠናክሩ መልእክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026