የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በቴክኖሎጂ ተደግፎ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ኤጀንሲው

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡- ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በአዳዲስ ቴክኖሎጂ ተደግፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።

በኤጀንሲው የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አስናቀች ሙህዬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ተቋሙ የተሟላ ሪፎርም ካደረገባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ የቴክኖሎጂ አሠራርን ማስፋት ነው።

በዚህም መሠረት አገልግሎት የሚሰጠው በሲስተም መሆኑን ጠቅሰው ይህም ከማዕከል ሆኖ ወረዳ ላይ እየተሰጡ ያሉ አገልግሎቶችን ማየት የሚያስችል ነው ብለዋል።

አሁን አገልግሎት እየሠጡ ካሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች የተሻለ እየበለፀገ መሆኑን ጠቁመው፤ በቅርቡ ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።

ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሠራሮች ውጤት እያስገኙ ነው ያሉት ዳይሬክተሯ፤ በቀጣይም እስከ ወረዳ ባሉ መዋቅሮች በአዳዲስ ቴክኖሎጂ የታገዙ ሥራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል።

ከብልሹ አሠራር ጋር በተያያዘ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በ17 ባለሙያ እና አንድ ባለጉዳይ ላይ የተለያየ ርምጃ መወሰዱንና በሕግ ሂደት ላይ የሚገኝ እንዳለም ጠቅሰዋል።

ከ2015 እስከ 2017 በጀት ዓመት በሐሰተኛ መረጃ ለመገልገል በሞከሩ 188 ተገልጋዮችና በአሠራር ጥሰት ደግሞ 589 ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ላይ ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።

ብልሹ አሠራርን በመከላከልና መቆጣጠር ሂደት የቴክኖሎጂ ሚና የጎላ መሆኑን ጠቁመው፤ ለአብነትም ድርጊቱ በየዓመቱ እየቀነሰ እንዲሄድ ማስቻሉን ተናግረዋል።

ተገልጋዮች ትክክለኛ መረጃና ማስረጃ አቅርበው አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ አስገንዝበው፤ ሕገ ወጥ አሠራር ሲያጋጥማቸው በ7533 ነጻ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡም ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026