የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በቴክኖሎጂ ተደግፎ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ኤጀንሲው

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡- ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በአዳዲስ ቴክኖሎጂ ተደግፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።

በኤጀንሲው የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አስናቀች ሙህዬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ተቋሙ የተሟላ ሪፎርም ካደረገባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ የቴክኖሎጂ አሠራርን ማስፋት ነው።

በዚህም መሠረት አገልግሎት የሚሰጠው በሲስተም መሆኑን ጠቅሰው ይህም ከማዕከል ሆኖ ወረዳ ላይ እየተሰጡ ያሉ አገልግሎቶችን ማየት የሚያስችል ነው ብለዋል።

አሁን አገልግሎት እየሠጡ ካሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች የተሻለ እየበለፀገ መሆኑን ጠቁመው፤ በቅርቡ ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።

ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሠራሮች ውጤት እያስገኙ ነው ያሉት ዳይሬክተሯ፤ በቀጣይም እስከ ወረዳ ባሉ መዋቅሮች በአዳዲስ ቴክኖሎጂ የታገዙ ሥራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል።

ከብልሹ አሠራር ጋር በተያያዘ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በ17 ባለሙያ እና አንድ ባለጉዳይ ላይ የተለያየ ርምጃ መወሰዱንና በሕግ ሂደት ላይ የሚገኝ እንዳለም ጠቅሰዋል።

ከ2015 እስከ 2017 በጀት ዓመት በሐሰተኛ መረጃ ለመገልገል በሞከሩ 188 ተገልጋዮችና በአሠራር ጥሰት ደግሞ 589 ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ላይ ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።

ብልሹ አሠራርን በመከላከልና መቆጣጠር ሂደት የቴክኖሎጂ ሚና የጎላ መሆኑን ጠቁመው፤ ለአብነትም ድርጊቱ በየዓመቱ እየቀነሰ እንዲሄድ ማስቻሉን ተናግረዋል።

ተገልጋዮች ትክክለኛ መረጃና ማስረጃ አቅርበው አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ አስገንዝበው፤ ሕገ ወጥ አሠራር ሲያጋጥማቸው በ7533 ነጻ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡም ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026