🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡-ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማሩ ባለፈ የምርምር ማዕከል በመሆን የትውልድና ሀገር ግንባታን የሚደግፉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ።
በዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አብዲ አህመድ ሀሰን (ዶ/ር)፤ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የእውቀት እና የምርምር ማዕከል በመሆን ለትውልድና ሀገር ግንባታ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ከመማር ማስተማሩ ባለፈ የክልሉን ብሎም የሀገርን እድገት መደገፍ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በተለይም በግብርና፣ ስነ- ህይወት፣ ምህንድስና፣ ፊዚክስ እና ሌሎችም ላይ የሚያተኩሩ ፅሁፎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ በማሳተም የእውቀትና የምርምር ማዕከል የመሆን ጥረቱን አጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል።
በማሕበረሰብ አገልግሎቱ በተለይም የትምህርት፣የጤና እና የሕግ አገልግሎቶች እንዲሁም የአቅም ግንባታ ድጋፎችን በማድረግ ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አንስተው፤ ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
አሁን ላይ በጅግጅጋ እና በሼኽ ሀሰን የበሬ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ካምፓሶቹ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ እንደሚገኘ ያነሱት የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንቱ፤ ሶስተኛውን ካምፓሱን በጎዴ ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026