🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡-ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማሩ ባለፈ የምርምር ማዕከል በመሆን የትውልድና ሀገር ግንባታን የሚደግፉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ።
በዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አብዲ አህመድ ሀሰን (ዶ/ር)፤ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የእውቀት እና የምርምር ማዕከል በመሆን ለትውልድና ሀገር ግንባታ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ከመማር ማስተማሩ ባለፈ የክልሉን ብሎም የሀገርን እድገት መደገፍ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በተለይም በግብርና፣ ስነ- ህይወት፣ ምህንድስና፣ ፊዚክስ እና ሌሎችም ላይ የሚያተኩሩ ፅሁፎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ በማሳተም የእውቀትና የምርምር ማዕከል የመሆን ጥረቱን አጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል።
በማሕበረሰብ አገልግሎቱ በተለይም የትምህርት፣የጤና እና የሕግ አገልግሎቶች እንዲሁም የአቅም ግንባታ ድጋፎችን በማድረግ ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አንስተው፤ ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
አሁን ላይ በጅግጅጋ እና በሼኽ ሀሰን የበሬ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ካምፓሶቹ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ እንደሚገኘ ያነሱት የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንቱ፤ ሶስተኛውን ካምፓሱን በጎዴ ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026