የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኮሪደር ልማቱ የድሬዳዋን የቱሪስትና የኢንቨስትመንት መዳረሻነት እያሳደገ ነው

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ የድሬዳዋ የኮሪደር ልማት የከተማዋን የቱሪስትና የኢንቨስትመንት መዳረሻነት እያሳደገው መሆኑ ተመለከተ።

የኮሪደር ልማት የከተሞችን ውበትና ገጽታ ከማሳደግ ባለፈ የየከተሞቹን የቱሪዝምና ኢንቨስትመንት መዳረሻነት እያሳደገው ይገኛል።

ወትሮም በቱሪስት መስህብነቷ የምትታወቀው ድሬደሠዳዋ የኮሪደር ልማቱ ተጨማሪ አቅም ፈጥሮላታል።


በአስተዳደሩ የፕሮጀክት ግንባታ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ወንድወሰን ጀንበር ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ የ11 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት የድሬዳዋን የኢንቨስትመንትና የቱሪስት መዳረሻነት አሳድጎታል።

በተለይም የኮሪደር ልማቱ ከባቡር መስመርና ተርሚናል ጋር ተጣጥሞ መሰራቱ የቱሪስት ፍሰቱ እንዲሳለጥ ማድረጉን አክለዋል።

የከተማዋን ማህበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ እንቅስቃሴዎች በማሳደግ ላይ የሚገኘው የኮሪደር ልማትን በማስቀጠልም ሁለተኛው ዙር የ16 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።


በእስካሁኑም ከሳብያን ድልድይ እስከ ነፃ ንግድ ቀጣና ባለው ጎዳና ላይ የእግረኛ፣ የብስክሌትና አካፋይ የአረንጓዴ ልማቶችን ከተቋማት ጋር በመናበብ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።


የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት የሙዚየም እና የባህል ቤቶች ቡድን መሪ ኤርሚያስ ታደሰ በበኩላቸው የኮሪደር ልማቱ 130 ዓመታት ካስቆጠረው የባቡር ቅርስ ጋር ተጣጥሞ በመሰራቱ የቱሪስት ፍሰትን በከፍተኛ መጠን ጨምሮታል ብለዋል።


በድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ጥናት መረጃ ዝግጅትና ፕሮሞሽን ቡድን አስተባባሪ አበራ መንግስቱ በበኩላቸው የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለስራ ምቹ በማድረጉ በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚሰማሩ ባለሃብቶች ቁጥር እንዲጨምር አድርጓል ነው ያሉት።

ለአብነትም በበጀት አመቱ ሩብ አመት ከ35 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ፍቃድ ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026