🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- በ2018 በጀት ዓመት እስካሁን በተሰራ ስራ 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ 7ሺህ 880 ቶን እሸት ቡና ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የመምሪያው ምክትል እና የቡናና ቅመማቅመም ዘርፍ ኃላፊ ከአብነህ ተስፋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል።

በዚህም እስካሁን 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን ገልጸው፤ አሁንም ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚላክ ቡና በተለያዩ ግብይቶች እየተሰበሰበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል 8 ነጥብ 9 ቶን የታጠበ እንዲሁም 343 ነጥብ 5 ቶን ያልታጠበ የተቀሸረ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ መላኩን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅትም ብክነት እንዳይኖር የደረሰ ቡና ከስር ከስር በቅንጅት እየተሰበሰበ መሆኑንም አመላክተዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025