🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- በ2018 በጀት ዓመት እስካሁን በተሰራ ስራ 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ 7ሺህ 880 ቶን እሸት ቡና ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የመምሪያው ምክትል እና የቡናና ቅመማቅመም ዘርፍ ኃላፊ ከአብነህ ተስፋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል።

በዚህም እስካሁን 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን ገልጸው፤ አሁንም ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚላክ ቡና በተለያዩ ግብይቶች እየተሰበሰበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል 8 ነጥብ 9 ቶን የታጠበ እንዲሁም 343 ነጥብ 5 ቶን ያልታጠበ የተቀሸረ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ መላኩን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅትም ብክነት እንዳይኖር የደረሰ ቡና ከስር ከስር በቅንጅት እየተሰበሰበ መሆኑንም አመላክተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026