🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ 10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትን በሚያጠናክር መልኩ ተከናውኖ በስኬት መጠናቀቁን የአፋር ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ገለጸ።
የአፋር ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ መሀመድ አሊ 10ኛው የከተሞች ፎረም መጠናቀቅን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ፎረሙ የአፋር ክልል እንግዳ ተቀባይነቱን በተግባር ያሳየበት እንደነበር ጠቁመው፤ በፎረሙ ለመታደም የመጡ እንግዶችን በተገቢው መንገድ ማስተናገድ መቻሉን አመላክተዋል።
በፎረሙ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልል የመጡ ከተሞች ስራዎቻቸውን እንዳቀረቡ ገልጸው፤ ተሞክሮቻቸውን በስፋት ማጋራት መቻላቸውን አስታውቀዋል።
ፎረሙ ከተሞች ያሉበትን የእድገት ደረጃ ያሳዩበት መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም ፎረሙ ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትን በሚያጠናክር መልኩ ተከናውኖ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸዋል።
በክልሉ የተከናወኑ የኮሪደር እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ልማት ስራዎች በመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች መጎብኘታቸውን አንስተዋል።
ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ክልሉ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው ከተሞች እድገትንና ብልጽግናን እንዲያረጋግጡ በጋራ ይሰራል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026