🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ 10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትን በሚያጠናክር መልኩ ተከናውኖ በስኬት መጠናቀቁን የአፋር ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ገለጸ።
የአፋር ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ መሀመድ አሊ 10ኛው የከተሞች ፎረም መጠናቀቅን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ፎረሙ የአፋር ክልል እንግዳ ተቀባይነቱን በተግባር ያሳየበት እንደነበር ጠቁመው፤ በፎረሙ ለመታደም የመጡ እንግዶችን በተገቢው መንገድ ማስተናገድ መቻሉን አመላክተዋል።
በፎረሙ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልል የመጡ ከተሞች ስራዎቻቸውን እንዳቀረቡ ገልጸው፤ ተሞክሮቻቸውን በስፋት ማጋራት መቻላቸውን አስታውቀዋል።
ፎረሙ ከተሞች ያሉበትን የእድገት ደረጃ ያሳዩበት መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም ፎረሙ ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትን በሚያጠናክር መልኩ ተከናውኖ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸዋል።
በክልሉ የተከናወኑ የኮሪደር እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ልማት ስራዎች በመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች መጎብኘታቸውን አንስተዋል።
ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ክልሉ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው ከተሞች እድገትንና ብልጽግናን እንዲያረጋግጡ በጋራ ይሰራል ብለዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026