የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ያለውን ጸጋ ለይቶ ጥቅም ላይ ለማዋል አመራሩ አሰራሩን መቀየርና የአስተሳሰብ አንድነትን ማጠናከር አለበት

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ያለውን ጸጋ ለይቶ ጥቅም ላይ ለማዋል አመራሩ ከተለመደ አሰራር መውጣትና የአስተሳሰብ አንድነት ማጠናከር እንዳለበት የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ፍቅሬ አማን ገለጹ።

"በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ለክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ ሁለተኛ ዙር ስልጠና ዛሬ በቦንጋ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል፡፡

የክልሉ ዋና መንግስት ተጠሪ ፍቅሬ አማን በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ያለውን የልማት አቅም ለመጠቀም አመራሩ የተለመደውን አሰራር መቀየርና የአስተሳሰብ አንድነትን መፍጠር አለበት፡፡


የክልሉ ዋነኛ የኢኮኖሚ ምንጭ የሆነውን የግብርና ዘርፍ በማዘመንና ውጤታማነቱን በማሳደግ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ ግብዓት እንዲሆን ትኩረት ሰጥቶ መስራት አለበትም ነው ያሉት፡፡

በግብርናው ዘርፍ ምርታማነትን ማሳደግ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን የማስጠበቅ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው፣ ጉዳዩ ከጂኦ ስትራቴጂክ ጉዳዮች ጋር በቀጥታ እንደሚገናኝም አንስተዋል።

ከአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ በሆነው ቱሪዝም ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት እመርታዊ ለውጦችን ማስመዝገብ እንደሚገባ ጠቁመው በክልሉ የሚገኙ የቱሪዝም ሃብቶችን በማልማት ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን ማሳደግ ይገባል ብለዋል፡፡


የከተማ ልማትን ጨምሮ ዋነኛ ሀገራዊና ክልላዊ የልማት መስኮችን ለማሳካት አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነት መፍጠርና ተቀራርቦ መስራትን እንዲያጠናክር ማስገንዘብ የስልጠናው አንዱ ዓላማ መሆኑን ተናግረዋል።

አብሮነትና የውስጠ ፓርቲ አንድነትን ማጠናከር እንዲሁም ተግባራትን በውጤታማነትና በቅንጅት መፈጸም ሌላኛው የስልጠናው ትኩረት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.