የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ ያለውን ጸጋ ለይቶ ጥቅም ላይ ለማዋል አመራሩ አሰራሩን መቀየርና የአስተሳሰብ አንድነትን ማጠናከር አለበት

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ያለውን ጸጋ ለይቶ ጥቅም ላይ ለማዋል አመራሩ ከተለመደ አሰራር መውጣትና የአስተሳሰብ አንድነት ማጠናከር እንዳለበት የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ፍቅሬ አማን ገለጹ።

"በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ለክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ ሁለተኛ ዙር ስልጠና ዛሬ በቦንጋ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል፡፡

የክልሉ ዋና መንግስት ተጠሪ ፍቅሬ አማን በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ያለውን የልማት አቅም ለመጠቀም አመራሩ የተለመደውን አሰራር መቀየርና የአስተሳሰብ አንድነትን መፍጠር አለበት፡፡


የክልሉ ዋነኛ የኢኮኖሚ ምንጭ የሆነውን የግብርና ዘርፍ በማዘመንና ውጤታማነቱን በማሳደግ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ ግብዓት እንዲሆን ትኩረት ሰጥቶ መስራት አለበትም ነው ያሉት፡፡

በግብርናው ዘርፍ ምርታማነትን ማሳደግ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን የማስጠበቅ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው፣ ጉዳዩ ከጂኦ ስትራቴጂክ ጉዳዮች ጋር በቀጥታ እንደሚገናኝም አንስተዋል።

ከአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ በሆነው ቱሪዝም ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት እመርታዊ ለውጦችን ማስመዝገብ እንደሚገባ ጠቁመው በክልሉ የሚገኙ የቱሪዝም ሃብቶችን በማልማት ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን ማሳደግ ይገባል ብለዋል፡፡


የከተማ ልማትን ጨምሮ ዋነኛ ሀገራዊና ክልላዊ የልማት መስኮችን ለማሳካት አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነት መፍጠርና ተቀራርቦ መስራትን እንዲያጠናክር ማስገንዘብ የስልጠናው አንዱ ዓላማ መሆኑን ተናግረዋል።

አብሮነትና የውስጠ ፓርቲ አንድነትን ማጠናከር እንዲሁም ተግባራትን በውጤታማነትና በቅንጅት መፈጸም ሌላኛው የስልጠናው ትኩረት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026