የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በጥራትና በፍጥነት አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡-መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ በጥራትና በፍጥነት አገልግሎት ለመስጠት እንዳስቻላቸው የሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ አስኪያጅ ከበደ ሻሜቦ ገለጹ።

በሀገር ደረጃ ከተነደፉ የተቋማት ማሻሻያ ፕሮግራም ውስጥ አንዱ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ነው።

20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ ጋዜጠኞች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ተገንብቶ ስራ የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የስራ እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል።


የሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ሻሜቦ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በቅርቡ ስራ የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ አሰራርን መሰረት ያደረገ ነው ።

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎቱ 60 አገልግሎቶችን መስጠት እንዲችል ሆኖ መገንባቱን ገልጸው፤ አሁን ላይ በሰባት ተቋማት 20 አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

ማዕከሉ የተገልጋዩን መረጃ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን አስችሏል ያሉት ስራ አስኪያጁ፤ ይህም የመረጃ ደህንነትንና ተጠያቂነትን ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

የማህበረሰቡን የአገልግሎት ጥያቄ በመመለስ የጥራት፣ የቅልጥፍና፣ የብልሹ አሰራር ችግሮችን በማስቀረት የአገልግሎት እርካታን ማሳደግ እያስቻለ መሆኑን ጠቁመዋል።


ህብረተሰቡ አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲያገኝ በማድረግ ጊዜንና ገንዘብን በመቆጠብ ረገድ አበርክቶው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም በክልሉ በሚገኙ ሌሎች ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች እንደሚቋቋሙ ስራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል።

አገልግሎቱ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም ተመርቆ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026