የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የባቡር አካዳሚው የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን ለማድረግ ጉልህ ድርሻ ያበረክታል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡-የባቡር አካዳሚው መገንባት የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን ለማድረግ እና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር ጉልህ ድርሻ እንደሚያበረክት የትርንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የትርንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሕሊና በላቸው በዛሬው እለት በቢሾፍቱ ከተማ ኪሎሌ ወረዳ የባቡር አካዳሚ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል፡፡


አካዳሚው የሚገነባው በቢሾፍቱ ከተማ ኪሎሌ ወረዳ ሲሆን፤ ግንባታው በ62 ሄክታር መሬት ላይ ያርፋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ዘመናዊ የትራንስፖርት እና የሎጂስቲክስ አገልግሎት ለኢኮኖሚያዊ እድገት ቁልፍ ግብዓት ነው ብለዋል፡፡

ዘርፉን ቀልጣፋ እና ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የሰላሳ ዓመታት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ፍኖተ ካርታ እና የአስር ዓመታት መሪ የልማት እቅድ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡

በዚህም ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ሰፊ የመንገድ እና የባቡር መሰረተ ልማቶችን በመስራት ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር የላቀ ሚና ስታበረክት መቆየቷን አስታውሰዋል፡፡

ዘመናዊ መንገዶችንና የባቡር መሠረተ ልማቶችን ከመዘርጋት ጎን ለጎን ኢንዱስትሪውን ሙሉ ለሙሉ ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ የባቡር አካዳሚ ማቋቋም ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

አካዳሚው ለኢንዱስትሪው የሰለጠነና የበቃ የሰው ሃይል በማፍራት ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡


አካዳሚው ስልጠናዎችን ከመስጠት ባሻገር ባቡር የሚገጣጠምበት፣ ጥገና የሚደረግበትና ባቡር እስከማምረት የሚደርስ ርዕይ እንዳለው ጠቁመዋል።

ለአጎራባች ሀገራት ባለሙያዎች ስልጠናዎችን በመስጠት የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆኖ እንደሚያገለግል እና ለስራ እድል ፈጠራ ሁነኛ አማራጭ እንደሚሆንም ገልጸዋል።

የባቡር አካዳሚው መገንባት የኢትዮጵያነ የማንሰራራት ጉዞ እውን ለማድረግ እና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር ጉልህ ድርሻ እንደሚያበረክት ነው የተናገሩት፡፡

የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሕሊና በላቸው በበኩላቸው፤ የባቡር ትራንስፖርት የወጪ እና ገቢ ምርቶችን እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳልጥ ተናግረዋል።


የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ እንደገለጹት፤ አካዳሚው ለከተማዋ በረከትና ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ ሆኖ ያገለግላል።

በመሆኑም አካዳሚው በተቀመጠለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026