የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በመናኸሪያው የተጀመረው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት እንግልትን አስቀርቷል

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ህዳር 17/2018(ኢዜአ)፦ በሆሳዕና ከተማ በህዝብ መናኸሪያ የተጀመረው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በተሳፋሪ ላይ ሲደርስ የነበረን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪና እንግልት ማስቀረቱን ተገልጋዮች ገለጹ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በበኩሉ ለህዝብ የሚሰጠው የትራንስፖርት አገልግሎት ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

መንግስት የትራንስፖርት ዘርፉን ማነቆዎች በመፍታት በህዝቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስና የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።


በዚህም በዲጂታል የታገዘ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት በህዝብ መናኸሪያዎች የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በማስጀመሩ ለውጥ እየተመዘገበ መጥቷል።

ኢዜአ በሆሳዕና ከተማ የህዝብ መናኸሪያ ተገኝቶ ያነጋገራቸው ተሳፋሪዎችና አሽከርካሪዎች በመናኸሪያው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ትርፍ ሰው ከመጫንና ተጨማሪ ክፍያን በማስቀረት በተሳፋሪ ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት ማስቀረቱን ተናግረዋል።

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ወንድም ዳኜ እንደገለጹት ፤ ከዚህ ቀደም በመናኸሪያው ትርፍ መጫንና ማስከፈልን ጨምሮ የተለያዩ እንግልቶች ይገጥሙ ነበር።


በዲጂታል የተደገፈ አገልግሎት መስጠት ከተጀመረ ወዲህ ከትራንስፖርት አገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ቀደም ሲል ሲገጥሙን የነበሩ ችግሮች ተፈተዋል፤ አሰራሩም በቀጣይ መጠናከር አለበት ብለዋል።

አቶ አየለ ጊፊሶ የተባሉ ተሳፋሪ በበኩላቸው እንዳሉት በመናኸሪያው የተጀመረው የኢ-ትኬቲንግ አገልግሎት ተገቢ ያልሆነ ክፍያን ከማስቀረት ባለፈ በተሳፋሪ ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት አስቀርቷል።


ይሁንና የዲጂታል አገልግሎቱ በወረዳ ባሉ መናኸሪያዎች ባለመጀመሩ ከታሪፍ ውጭ ማስከፈል አሁንም እንዳለ ጠቅሰው ዲጂታል ትራንስፖርት አገልግሎቱ በሁሉም መዋቅሮች እንዲስፋፋ ጠይቀዋል፡፡

መንግስት ባስቀመጠው የታሪፍ ክፍያ መሰረት ማህበረሰቡን እያገለገሉ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በመናኸሪው የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪው ግዛቸው ሃይሉ ናቸው።


የኢ-ቲኬቲንግ መጀመር ከተራ አስከባሪዎች ጋር የነበራቸውን ያለመግባባት ችግር መፍታቱን ተናግረዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በክልሉ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎትን ዲጂታላይዝ በማድረግ የተመዘገበውን ውጤት ለማጠናከር ይሰራል ብለዋል።


የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በክልሉ በሚገኙ 23 መናኸሪያዎች ተግባራዊ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡

አገልግሎቱ በትራንስፖርት ዘርፍ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን ከመቀነስ አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰው፣ በቀጣይም አገልግሎቱን በሁሉም መናኸሪያዎች የማስፋት ሥራ ይሰራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026