🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው የበጋ መስኖ ልማት ሥራ 65 ሺህ 347 ሔክታር በተለያዩ ሰብሎች እንደሚለማ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ባበከር ኸሊፋ ተናገሩ።
ኃላፊው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች የበጋ መስኖ ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል።

ከበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጋር በተያያዘ በክልሉ ለስንዴ ልማት ተስማሚ ተፈጥሯዊ ሁኔታ ባላቸው ወረዳዎች 1 ሺህ 202 ሔክታር ይለማል ብለዋል።
እስካሁን እየተከናወነ ባለው ሥራም 445 ሔክታር በበጋ ስንዴ ዘር መሸፈኑን አረጋግጠዋል።
ከዚህ ውስጥ በክላስተር እየለማ ያለው 222 ሔክታር መሆኑንም ጠቁመዋል።
በዘንድሮው የበጋ መስኖ ልማት ሥራ ለማልማት ከታቀደው 65 ሺህ 347 ሔክታር ውስጥ 10 ሺህ 557 ሔክታሩ በክላስተር እንደሚለማም ነው ያመላከቱት።

እስካሁን ባለው የበጋ መስኖ ልማት ሥራ 9 ሺህ 487 ሔክታር በተለያዩ ሰብሎች ዘር መሸፈኑን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ የመስኖ ተጠቃሚዎች ቁጥር 13 ሺህ 386 መሆኑንም ነው የገለጹት።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026