🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው የበጋ መስኖ ልማት ሥራ 65 ሺህ 347 ሔክታር በተለያዩ ሰብሎች እንደሚለማ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ባበከር ኸሊፋ ተናገሩ።
ኃላፊው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች የበጋ መስኖ ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል።

ከበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጋር በተያያዘ በክልሉ ለስንዴ ልማት ተስማሚ ተፈጥሯዊ ሁኔታ ባላቸው ወረዳዎች 1 ሺህ 202 ሔክታር ይለማል ብለዋል።
እስካሁን እየተከናወነ ባለው ሥራም 445 ሔክታር በበጋ ስንዴ ዘር መሸፈኑን አረጋግጠዋል።
ከዚህ ውስጥ በክላስተር እየለማ ያለው 222 ሔክታር መሆኑንም ጠቁመዋል።
በዘንድሮው የበጋ መስኖ ልማት ሥራ ለማልማት ከታቀደው 65 ሺህ 347 ሔክታር ውስጥ 10 ሺህ 557 ሔክታሩ በክላስተር እንደሚለማም ነው ያመላከቱት።

እስካሁን ባለው የበጋ መስኖ ልማት ሥራ 9 ሺህ 487 ሔክታር በተለያዩ ሰብሎች ዘር መሸፈኑን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ የመስኖ ተጠቃሚዎች ቁጥር 13 ሺህ 386 መሆኑንም ነው የገለጹት።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026