የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

መስኖን ተጠቅመን ባለማነው አትክልትና ፍራፍሬ ተጠቃሚ ሆነናል-አርሶ አደሮች

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ የበጋ መስኖን በመጠቀም ባለሙት አትክልትና ፍራፍሬ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን በልማቱ የተሳተፉ አርሶ አደሮች ገለጹ።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ የነበራቸው አርሶ አደሮች እንደገለፁት፤ መስኖን በመጠቀም ባለሙት አትክልትና ፍራፍሬ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን አሳድገዋል።

የገንዳ ውኃ ከተማ ነዋሪው አርሶ አደር አደም ሁሴን ለኢዜአ እንደገለጹት መስኖን በመጠቀም ቋሚ አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ይገኛሉ።


ባለፉት ቅርብ ዓመታት ያለሙት የማንጎ፣ የፓፓያ፣ የዘይቱን፣ የሙዝ፣ የሎሚና የሌሎች የፍራፍሬ ዝርያዎች ምርት መስጠት በመጀመራቸው ባለፈው ዓመት ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በዘንድሮ ዓመትም ካለፈው የተሻለ ገቢ ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ጠቁመው ከሚያገኙት ገቢም በባንክ በመቆጠብ በቀጣይ ወደ ተሻለ ኢንቨስትመንት ለመግባት ፍላጎቱ እንዳላቸውም አስረድተዋል።

ሌላኛው የዚሁ ከተማ ነዋሪ አርሶ አደር ሙሀመድ ገደፋው በበኩላቸው፤ የፍራፍሬ ልማት በቅርብ ጊዜ የተጀመረ ቢሆንም የሚሰጠውን ጥቅም በመረዳት በብዛት የማልማት ስራ እየሰራሁ ነው ብለዋል።


በሩብ ሄክታር ማሳቸው ላይ ባለሙት ፍራፍሬ በዓመት ከ150 ሺህ ብር በላይ ገቢ እያገኙ መሆኑን ጠቁመው የፍራፍሬ ልማቱን ወደ አንድ ሄክታር ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።

ቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት አዋጭ መሆኑን በመገንዘብ አንድ ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ በዘርፉ መሰማራቱን የገለፀው ደግሞ የመተማ ዮሃንስ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት ሰውበሰው አለነ ነው።


ከሁለት ሄክታር በላይ መሬት ላይ ያለማው የማንጎ፣ የፓፓያ፣ የሎሚ፣ የብርቱካንና የዘይቱን ተክል ምርት መስጠት በመጀመሩ እስካሁን ያወጣውን ወጪ በዘንድሮው የምርት ሽያጭ እንደሚመልስም ተስፋ አድርጓል።

በምእራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ባለሙያ አቶ አስናቀው አራጋው እንዳሉት፤ በዞኑ አንድ ሺህ 200 ሄክታር መሬት በፍራፍሬና ቋሚ አትክልት ለምቷል።

በዚህም 35 አርሶ አደሮችንና ባለሃብቶችን በማሳተፍ በተካሄደው የፍራፍሬ ልማት ባለፈው ዓመት ከ170 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።


በተያዘው በጀት ዓመትም ከ200 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ አስረድተዋል።

እየተገኘ ያለውን ጥቅም በቀጣይ ለማስፋትም ዘንድሮ ከ250 ሺህ በላይ አዳዲስና ቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል ፍል የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በተጨማሪም በዞኑ የሚካሄደው የፍራፍሬ ልማት ለወጣቱ የስራ እድል መፍጠሪያ ዋና አማራጭ ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

አርሶ አደሮች የሚፈልጉትን የፍራፍሬ ችግኝ በቀበሌና በወረዳ ማዕከላት ለማሰራጨት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026