የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዓባይ ተፋሰስ ሀገራትን የጋራ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ነው 

Dec 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን እና የዓባይ ተፋሰስ ሀገራትን የጋራ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ የኃይል ማመንጫ ግድቦች የውሃ አስተዳደር በዕውቀትና በከፍተኛ ኃላፊነት የሚመራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የሀገራት መሪዎች፣ የቀጣናዊ፣ አሕጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት መመረቁ ይታወቃል።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)÷ የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ስኬት ለዘመናት የልማት ቁጭት መልስ የሰጠ የኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት የብሩህ ተስፋ ብስራት ነው ብለዋል።

ከግድቡ የሚገኘው ኃይል የኢኮኖሚውን መዋቅራዊ ሽግግር በማሳለጥና ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን በማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በቀጣናው የፈጠረችው ከፍተኛ የኃይል ትስስር የአፍሪካን የኢኮኖሚ ውህደት ለማረጋገጥ የራሱን መሰረት መጣሉን ተናግረዋል።

የሕዳሴ ግድብ በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት የሚከሰተውን ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ በመቀነስና በበጋ ወራት አስተማማኝ የውሃ ፍሰት በማስገኘት ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል።

በሌላ በኩል በግብጽ አማካይነት በአንድ በኩል ውሃ ተያዘብን በሌላ በኩል ጎርፍ ተለቀቀብን በሚል የሚናፈሱ መረጃዎች እርስ በርስ የሚጣረሱና መሰረተ ቢስ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ የኃይል ማመንጫ ግድቦች የውሃ አስተዳደርና ውሃ አለቃቀቅ ሥርዓት በዕውቀትና በከፍተኛ ኃላፊነት እየተመራ መሆኑን አስገንዝበዋል።


የሕዳሴ ግድብ የውሃ አስተዳደር የኢትዮጵያን ጥቅም በማስከበር የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራትን በማይጎዳ መንገድ በብሔራዊ ቴክኒካል ኮሚቴ እየተመራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ስንገነባ እኛን ለመጉዳት ነው ሲሉ የነበሩ አካላት ግድቡ እውን ከሆነ በኋላ አካሄዳቸው ከፍተኛ ውሃ እየተለቀቀብን ነው ወደሚል ሀሰተኛ ትርክት ተቀየረ ሲሉም ገልጸዋል።

ሕዳሴ ግድብ የዓባይን ውሃ በተገቢው መንገድ በማስተዳደር የኢትዮጵያንና የታችኞቹን የተፋሰስ ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ በውሃ ሃብቷ እንዳትጠቀም ለዘመናት ሲሸረብባት የነበረውን ሴራና ትርክት በመቀልበስ የጋራ ተጠቃሚነት መርህን ማስረጽ እንደቻለች ተናግረዋል።

በኢትዮጵያውያን አንጡራ ሃብት የተገነባውን ሕዳሴ ግድብን በጋራ እናስተዳድር የሚል ሉዓላዊነትን የሚዳፈር የቅዠት እሳቤም ተቀባይነት የሌለው አካሄድ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለፍትሐዊ ተጠቃሚነት መርህ የምትገዛ ሀገር ናት ያሉት ሚኒስትሩ፤ ግብጽና ሱዳን በዓባይ ውሃና በሕዳሴ ግድብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የጸና አቋሟን በተግባር እያሳየች ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026