የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በከተሞች መሰረተ ልማትን በማሟላት ለነዋሪዎች ምቹ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል - ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ

Dec 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ከሚሴ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፡-በሀገሪቱ ከተሞች መሰረተ ልማትን በማሟላት ለነዋሪዎች እና ለኢንቨስትመንት ምቹ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እና ሌሎች የፌዴራል ከፍተኛ አመራሮች በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ከሚሴና ጨፋ ሮቢት ከተሞች የልማት ሥራ እንቅስቃሴዎችን ዛሬ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።


በጉብኝቱ ወቅት ሚኒሰትሯ እንዳመለከቱት፤ በከተሞች የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ የመሰረት ልማት ግንባታዎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ።

በሀገሪቱ ከተሞች መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ለነዋሪዎች እና ለኢንቨስትመንት ምቹ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የተጀመሩ የልማት ስራዎች አበረታች መሆናቸውንና ይበልጥ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል።

የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው ፣ በዞኑ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

በዞኑ ከተሞችም መሰረተ ልማትን በማሟላት ለነዋሪዎች፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።

በጉብኝቱም የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026