🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ሮቤ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪዎች ብሎም ለቱሪስቶች በይበልጥ ምቹ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ።
የሮቤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ኤሊያስ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢኮኖሚና የቱሪስት ማዕከል የሆነችውን ሮቤ ከተማን በይበልጥ ምቹና ውብ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው።

በዚህም እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት መካከል የኮሪደር ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በከተማዋ 7 ነጥብ 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ለመሥራት መታቀዱን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፤ እስካሁን 5 ነጥብ 56 ኪሎ ሜትር መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።

ቀሪውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የከተማዋ ኮሪደር ልማት የእግረኛና የብስክሌት መንገድን ጨምሮ ፋውንቴኖችና አደባባዮች ማካተቱን አብራርተዋል።
ከኮሪደር ልማቱ ጋር በተያያዘም ከ400 ለሚልቁ ሰዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ነው ያመላከቱት።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026