🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ሮቤ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪዎች ብሎም ለቱሪስቶች በይበልጥ ምቹ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ።
የሮቤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ኤሊያስ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢኮኖሚና የቱሪስት ማዕከል የሆነችውን ሮቤ ከተማን በይበልጥ ምቹና ውብ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው።

በዚህም እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት መካከል የኮሪደር ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በከተማዋ 7 ነጥብ 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ለመሥራት መታቀዱን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፤ እስካሁን 5 ነጥብ 56 ኪሎ ሜትር መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።

ቀሪውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የከተማዋ ኮሪደር ልማት የእግረኛና የብስክሌት መንገድን ጨምሮ ፋውንቴኖችና አደባባዮች ማካተቱን አብራርተዋል።
ከኮሪደር ልማቱ ጋር በተያያዘም ከ400 ለሚልቁ ሰዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ነው ያመላከቱት።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025