🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ሮቤ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪዎች ብሎም ለቱሪስቶች በይበልጥ ምቹ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ።
የሮቤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ኤሊያስ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢኮኖሚና የቱሪስት ማዕከል የሆነችውን ሮቤ ከተማን በይበልጥ ምቹና ውብ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው።

በዚህም እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት መካከል የኮሪደር ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በከተማዋ 7 ነጥብ 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ለመሥራት መታቀዱን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፤ እስካሁን 5 ነጥብ 56 ኪሎ ሜትር መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።

ቀሪውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የከተማዋ ኮሪደር ልማት የእግረኛና የብስክሌት መንገድን ጨምሮ ፋውንቴኖችና አደባባዮች ማካተቱን አብራርተዋል።
ከኮሪደር ልማቱ ጋር በተያያዘም ከ400 ለሚልቁ ሰዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ነው ያመላከቱት።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026