የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኮሪደር ልማቱ ሮቤ ከተማን ለነዋሪዎችና ለቱሪስቶች ምቹ እንድትሆን እያስቻለ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ሮቤ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪዎች ብሎም ለቱሪስቶች በይበልጥ ምቹ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ።

የሮቤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ኤሊያስ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢኮኖሚና የቱሪስት ማዕከል የሆነችውን ሮቤ ከተማን በይበልጥ ምቹና ውብ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው።


በዚህም እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት መካከል የኮሪደር ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በከተማዋ 7 ነጥብ 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ለመሥራት መታቀዱን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፤ እስካሁን 5 ነጥብ 56 ኪሎ ሜትር መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።


ቀሪውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

የከተማዋ ኮሪደር ልማት የእግረኛና የብስክሌት መንገድን ጨምሮ ፋውንቴኖችና አደባባዮች ማካተቱን አብራርተዋል።

ከኮሪደር ልማቱ ጋር በተያያዘም ከ400 ለሚልቁ ሰዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ነው ያመላከቱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.