🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ሮቤ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪዎች ብሎም ለቱሪስቶች በይበልጥ ምቹ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ።
የሮቤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ኤሊያስ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢኮኖሚና የቱሪስት ማዕከል የሆነችውን ሮቤ ከተማን በይበልጥ ምቹና ውብ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው።

በዚህም እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት መካከል የኮሪደር ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በከተማዋ 7 ነጥብ 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ለመሥራት መታቀዱን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፤ እስካሁን 5 ነጥብ 56 ኪሎ ሜትር መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።

ቀሪውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የከተማዋ ኮሪደር ልማት የእግረኛና የብስክሌት መንገድን ጨምሮ ፋውንቴኖችና አደባባዮች ማካተቱን አብራርተዋል።
ከኮሪደር ልማቱ ጋር በተያያዘም ከ400 ለሚልቁ ሰዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ነው ያመላከቱት።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026