የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ማዕከሉ ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ ሰብሎችን እያስተዋወቀ ነው

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፡- የአሶሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ የማሽላ እና አኩሪ አተር ዝርያዎችን እያስተዋወቀ ነው።

በማዕከሉ በምርምር የተሻሻሉ የማሽላ እና የአኩሪ አተር ሰብሎች በማዕከሉና በአርሶ አደር ማሳ በኩታ ገጠም በማልማት የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የማዕከሉ ዳይሬክተር ደስታ በቀለ ለኢዜአ ተናግረዋል።

በዚህም መሠረት በምርምር ማዕከሉ በ81 ሔክታር ላይ በኩታ ገጠም ማሽላ እየለማ መሆኑን ጠቁመዋል።

እነዚህ በምርምር የተሻሻሉት ‘አሶሳ አንድ’ እና ‘አሶሳ ሁለት’ የተሰኙ የማሽላ ዝርያዎች በአርሶ አደር ማሳ ላይ በሔክታር እስከ 35 ኩንታል ምርት እንደሚሰጡ ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል በአሶሳ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በ32 ሔክታር ላይ በኩታ ገጠም የለማ የአኩሪ አተር ሰብልን ለአርሶ አደሩ እየተዋወቀ ነው ብለዋል።

እስካሁን ጥቅም ላይ እየዋለ ያለውን የግሻማ አኩሪ አተር ዝርያ የሚተኩ ‘አንድነት’ እና ‘ጣና በለስ’ የተሰኙ ዝርያዎችን በዚህ ዓመት በማልማት ለአርሶ አደሩ የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

እነዚህ የአኩሪ አተር ዝርያዎች መካከለኛ መድረሻ ጊዜ ያላቸው፣ ምርታማነታቸው የተረጋገጠ፣ ከ700 እስከ 1 ሺህ 860 ሜትር ከባሕር ጠለል በላይ የሚላመዱና በሽታን የመቋቋም ዐቅማቸውም ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።

88 በማሽላ እንዲሁም 76 አርሶ አደሮች በአኩሪ አተር ዝርያ ማልማትና ማስተዋወቅ ሥራው ላይ ተሳታፊ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

በአጠቃላይ ማዕከሉ በተለያዩ ሰብሎችና እንስሳት ዘርፎች ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ ሥራዎች በተለያዩ ወረዳዎች እያከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.