🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፡- የአሶሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ የማሽላ እና አኩሪ አተር ዝርያዎችን እያስተዋወቀ ነው።
በማዕከሉ በምርምር የተሻሻሉ የማሽላ እና የአኩሪ አተር ሰብሎች በማዕከሉና በአርሶ አደር ማሳ በኩታ ገጠም በማልማት የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የማዕከሉ ዳይሬክተር ደስታ በቀለ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በዚህም መሠረት በምርምር ማዕከሉ በ81 ሔክታር ላይ በኩታ ገጠም ማሽላ እየለማ መሆኑን ጠቁመዋል።
እነዚህ በምርምር የተሻሻሉት ‘አሶሳ አንድ’ እና ‘አሶሳ ሁለት’ የተሰኙ የማሽላ ዝርያዎች በአርሶ አደር ማሳ ላይ በሔክታር እስከ 35 ኩንታል ምርት እንደሚሰጡ ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል በአሶሳ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በ32 ሔክታር ላይ በኩታ ገጠም የለማ የአኩሪ አተር ሰብልን ለአርሶ አደሩ እየተዋወቀ ነው ብለዋል።
እስካሁን ጥቅም ላይ እየዋለ ያለውን የግሻማ አኩሪ አተር ዝርያ የሚተኩ ‘አንድነት’ እና ‘ጣና በለስ’ የተሰኙ ዝርያዎችን በዚህ ዓመት በማልማት ለአርሶ አደሩ የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አመላክተዋል።
እነዚህ የአኩሪ አተር ዝርያዎች መካከለኛ መድረሻ ጊዜ ያላቸው፣ ምርታማነታቸው የተረጋገጠ፣ ከ700 እስከ 1 ሺህ 860 ሜትር ከባሕር ጠለል በላይ የሚላመዱና በሽታን የመቋቋም ዐቅማቸውም ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።
88 በማሽላ እንዲሁም 76 አርሶ አደሮች በአኩሪ አተር ዝርያ ማልማትና ማስተዋወቅ ሥራው ላይ ተሳታፊ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ማዕከሉ በተለያዩ ሰብሎችና እንስሳት ዘርፎች ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ ሥራዎች በተለያዩ ወረዳዎች እያከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026